Fana: At a Speed of Life!

የነዳጅ ድጎማን ለማግኘት ከ134 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች ተመዝግበዋል- ኢትዮ ቴሌኮም

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የታለመለት የነዳጅ ድጎማ አገልግሎት ለማግኘት 134 ሺህ 684 ተሽከርካሪዎች መመዝገባቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬ ህይወት ታምሩ በሰጡት ማብራሪያ÷ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በድጎማው ተጠቃሚ…

አቶ ኦርዲን በድሪን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ሥራ ኃላፊዎች በሐረር ከተማ  ችግኝ ተከሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ በሐረር ከተማ ባሕል ማዕከል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የችግኝተከላ መርሐ ግብር አካሂደዋል፡፡ ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎን የአቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት…

የደቡብ ክልል ምክር ቤት ከ46 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ሆኖ የቀረበውን የክልሉ መንግስት የ2015 በጀት አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ምክር ቤት ከ46 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ሆኖ የቀረበውን የክልሉ መንግስት የ2015 በጀት አጸደቀ፡፡ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ 46 ቢሊየን 316 ሚሊየን 524 ሺ 693 ብር በጀትን…

በአማራ ክልል በኢንቨስትመንት ላይ ያሉ ማነቆዎችን ለመፍታት የሚያስችል ምክክር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በኢንቨስትመንት ላይ ያሉ ማነቆዎችን ለመፍታት የሚያስችል ምክክር ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ በተገኙበት ተካሂዷል ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ከደሴ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ ከደቡብ እና ሰሜን ወሎ ዞን የስራ ሃላፊዎች…

የዩክሬንን እህል ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ከሩሲያ ጋር ስምምነት መደረሱን ቱርክ አስታወቀች

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቱርክ በጥቁር ባሕር የዩክሬንን እህል ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ከሩሲያ ጋር ስምምነት መደረሱን አስታወቀች። የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎም በዛሬው እለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በተገኙበት በሩሲያ እና ዩክሬን…

የሲዳማ ክልል የ2014 በጀት አመት የስራ አፈፃፀምን እየገመገመ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል የ2014 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም እየገመገመ ነው፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ የ2014 ዓ.ም የስራ አፈፃፀምን እየገመገሙ ሲሆን÷ የክልሉ የየቢሮ የስራ ሃላፊዎች የ2014 ዓ.ም የአፈፃፀም ሪፖርት እያቀረቡ ነው፡፡…

በ2015 ዓ.ም. ከወጪ ንግድ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል- የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀጣይ በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማምጣት መታቀዱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ዛሬ እየተከበረ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ወጪ ንግድ ቀን አስመልክቶ “የኢትዮጵያን ባለ ልዩ ጣዕም ምርት ይግዙ” በሚል መሪ ሐሳብ…

በደቡብ ክልል በበጀት አመቱ ከ300 ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳ ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2014 በጀት ዓመት በደቡብ ክልል ከ300 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳ ገለጹ፡፡ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 1ኛ ዓመት የሥራ…

 በመተከል ዞን ድባጤ ወረዳ 21 የታጠቁ የሽፍታ ቡድን አባላት በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን ሰጡ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን ድባጢ ወረዳ ጫካ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 21 የታጠቁ የሽፍታ ቡድን አባላት በሰላማዊ መንገድ እጅ መስጠታቸው ተገለጸ፡፡ የቡድኑ አባላት በቀጠናው እየተካሄደ ካለው ሕግ ማስከበር ተግባር ጋር ተያይዞ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው…

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 200 ሺህ ብር ጉቦ ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዟል የተባለ የስራ ሀላፊ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 አገልግሎትን በገንዘብ ለመሸጥ 200 ሺህ ብር ጉቦ ሲቀበል ተገኝቷል የተባለ የቤቶች ጽህፈት ቤት ኃላፊ እጅ ከፍንጅ መያዙን ፖሊስ ገለፀ፡፡ በክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና የትራፊክ…