Fana: At a Speed of Life!

ለማረፍ ሲዘጋጅ ጭስ የታየበት አውሮፕላን በተሳካ ሁኔታ አርፏል- የኢትዮጵያ አየር መንገድ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፊያ ለማረፍ በዝግጅት ላይ ሳለ ጭስ የታየበት አውሮፕላን በሰላም ማረፉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ፡፡ ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET248 አውሮፕላን…

አቶ አደም ፋራህ በጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር በነበሩት ጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን…

ም/ጠ/ ሚ ተመስገን በጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር በነበሩት ጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት÷ የኢትዮጵያ ኅብረት…

በሙስና ወንጀል የተከሰሱት የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች በስር ፍርድ ቤት የተጣለባቸው የቅጣት ውሳኔ ተሻረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች በተከሰሱበት ከሲሚንቶ ግዢ ጋር የተያያዘ የሙስና ወንጀል በስር ፍርድ ቤት የተጣለባቸው የቅጣት ውሳኔ ተሻረ። ተከሳሾቹ ላይ በስር ፍርድ ቤት ተወስኖ በነበረው የቅጣት ውሳኔ ቅር በመሰኘት ዐቃቤ ሕግ…

በአረንጓዴ ዐሻራ ሥራና ሐይማኖታዊ አስተምኅሮ ለበርካታ ዓመታት ያገለገሉት አባ መፍቀሬ ሰብዕ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐይማኖታዊ አስተምኅሮ፣ በብዝኃ ሕይወት ጥበቃ ሥራ እና አንድነትን በማስተማር ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን አድባራት ያገለገሉት አባ መፍቀሬ ሰብዕ ኪዳነወልድ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ፡፡ በ1921 ዓ.ም…

ኢትዮጵያ ላስጠለለቻቸው ፍልሰተኞች መሠረታዊ አገልግሎት እየሰጠች ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የተጠለሉ ፍልሰተኞች መሠረታዊ አገልግሎት እያገኙ መሆኑን አምባሳደር ጸጋአብ ክበበው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ አብራሩ፡፡ በጄኔቫ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ጸጋአብ ክበበው…

በአማራ ክልል ለ2 ሚሊየን 982 ሺህ ሕጻናት የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ2 ሚሊየን 982 ሺህ ሕጻናት የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) መከላከያ ክትባት መስጠት መቻሉን የአማራ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ ከ4 ሚሊየን በላይ ሕጻናትን ለመድረስ ታቅዶ ከመስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ክትባቱ…

ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከማንቼስተር ዩናይትድ አምባሳደርነት ሊነሱ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞው ስኬታማ አሰልጣኝና ባለፉት ዓመታት የቡድኑ ዓለም አቀፍ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በዓመቱ መጨረሻ ከኃላፊነታቸው እንደሚሰናበቱ ተሰምቷል፡፡ ሰር አሌክስ ከፈረንጆቹ 2013 ጀምሮ ቀያይ…

የመሬት ይዞታ መረጃ አያያዝን ማዘመን የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን ይቀርፋል- ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባና የመረጃ ሥርዓቱን ዘመናዊ ማድረግ በዘርፉ ያሉ ኢ-ፍትሐዊ አሠራሮችን በማስቀረት የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን ለማስወገድ ያስችላል ሲሉ የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ…

በ32 ቀናት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ከ828 ቢሊየን ብር በላይ ዝውውር ተፈጸመ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከነሐሴ 30 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 26 ቀን 2017 ዓ.ም ባሉት ቀናት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች በተከናወኑ ግብይቶች 828 ቢሊየን 549 ሚሊየን 614 ሺህ 770 ብር ዝውውር መፈጸሙ ተገለፀ፡፡ ከላይ በተጠቀሰው…