Fana: At a Speed of Life!

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በዋግኽምራ ዞን ለ42 ሺህ ወገኖች ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዋግኽምራ ዞን ለሚገኙ 42 ሺህ ወገኖች የሚውል ምግብና ምግብ ነክ ያልሆነ ድጋፍ ማድረጉን የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ በዞኑ ዝቋላ ወረዳ፣ ፅፅቃ ከተማ እና አካባቢው ለሚገኙ እና ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው 30 ሺህ ወገኖች…

በሪል እስቴቶች የሚገነቡ ቤቶች ከዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ታሳቢ ማድረግ አለባቸው- የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሪል እስቴቶች የሚገነቡ ቤቶች ከፍተኛ ገቢ ያላቸውን ብቻ ሳይሆን መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ታሳቢ ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው ተገለጸ፡፡ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ካሉ የሪል እስቴት አልሚዎች ጋር ዘርፉን…

ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ጋር ተወያይዋል፡፡ በውይይታቸው ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ የጃፓን ሕዝብ እና መንግሥት ለአማራ ክልል ልማት እያደረጉት ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡ አምባሳደር ኢቶ…

በደቡብ ክልል በ679 ሚሊየን ብር የተገነቡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት ተመረቁ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ679 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች መመረቃቸውን የደቡብ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ ገለፀ። ተገንብተው ከተጠናቀቁ ከ12 በላይ ፕሮጀክቶች መካከል በወላይታ ዞን የጠበላ ከተማ ኮንስትራክሽንና…

የሰላም ስምምነቱ በታቀደለት መንገድ እንዲፈጸም መንግሥት እየሠራ ነው- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

በደቡብ አፍሪካ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በታቀደለት መንገድ እንዲሄድ ለማድረግ የኢትዮጵያ መንግሥት እየሠራ ነው። በዚህም መሠረት በመከላከያ ሥር ወዳለው አብዛኛውየትግራይ አካባቢ እርዳታ እንዲደርስ እየተደረገ ነው። ወደተለቀቁት አካባቢዎች መሠረታዊ አገልግሎቶች ቀስ በቀስ እየተጀመሩ ነው።…

በጭሮ ወረዳ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ ወረዳ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የስምንት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡ አደጋው የተከሰተው ከሐረር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከመኤሶ ሁሴን ወደ ጭሮ በመጓዝ ላይ…

የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት የማድረጉ ሂደት በውስን የውጭ ባንኮች ብቻ እንደሚጀምር ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፉን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት የማድረጉ ሂደት ውስን ቁጥር ባላቸው የውጭ ባንኮች ብቻ የሚጀመር መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ተቋማት ሱፐርቪዥን ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ…

11 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በተባሉ ግለሰቦች፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ደላሎች ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ፖሊስ ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የልማት ተነሺ ነን በማለት ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት 11 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በተባሉ ዘጠኝ ግለሰቦች፣ ወንጀሉ እንዲፈፀም ሁኔታዎችን አመቻችተዋል በተባሉ ሦስት የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና በ3 ደላሎች ላይ ምርመራ እያካሄደ…

የዳያስፖራውን ሁሉአቀፍ ተሳፎ የሚያሳድጉ ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጁ ነኝ- ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት በሚያቀርበው ጥያቄ መሰረት የዳያስፖራውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ የሚያሳድጉ ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጁ መሆኑን የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ አስታወቀ፡፡ የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች…

የወባ በሽታ ስርጭት እየጨመረ በመምጣቱ ህብረተሰቡ የመከላከያ መንገዶችን እንዲተገብር ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የወባ በሽታ ስርጭት እየጨመረ በመምጣቱ ህብረተሰቡ የመከላከያ መንገዶችን በመተግበር ራሱን እንዲጠብቅ የጤና ሚኒስቴር አሳሰበ፡፡ የወባ በሽታን ለመከላከልም÷ አጎበር መጠቀም፣ የመኖሪያ ስፍራዎችን ንጽህና መጠበቅ እና የጸረ ወባ ኬሚካል ማስረጨት ይገባል…