Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

በአፋር ክልል ለአቅመ ደካሞች የሚውል የ21 ሚሊየን ብር ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን ለአፋር ክልል በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአቅመ ደካሞች የሚውል የ21 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ድጋፉን የተረከቡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ÷ለተቸገሩ እና ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ…

የአማራ ክልልን ከስጋት ወጥቶ ወደ ብልጽግና ለማሻገር የክልሉ አመራር ቁርጠኛነቱን እያሳየ ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልልን ከግጭትና ከጸጥታ ስጋት ወጥቶ ወደ ብልጽግና ለማሻገር የክልሉ አመራር ቁርጠኛነቱን በተግባር እያሳየ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የክልሉ የ25 ዓመት የማክሮ ኢኮኖሚ…

ተቋማቱ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስቴር እና የገቢዎች ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት የችግኝ ተከላ በማካሄድ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ። ተቋማቱ ‘የምትተክል ሀገር፤ የሚያጸና ትውልድ’ በሚል እየተካሄደ በሚገኘው የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ተሳትፎ በማድረግ ችግኝ…

የፋይንቴክ ኩባንያዎች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፋይናንስ ኢንቨስመንት ለመሰማራት ፍላጎት እንዳሳደረባቸው ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በፋይናንስ ኢንቨስመንት ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት እንዳሳደረባቸው የተለያዩ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ቴክኖሎጂ አቅራቢ ኩባንያዎች (ፋይንቴክ) ገለጹ። የፋይናንስ ተቋማት ቴክኖሎጂ አቅራቢና አማካሪ ዓለም አቀፍ…

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2ኛ ዙር የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2ኛ ዙር "የትምህርት ለትውልድ" ንቅናቄ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው። በንቅናቄ መድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው፣ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንዲሁም ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና…

በአንድ ጀምበር 600 ሚሊየን ችግኝ የመትከል ዕቅድ እንዲሳካ ክልሎች ዝግጅት ማድረጋቸውን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀገር አቀፍ ደረጃ የተያዘው በአንድ ጀምበር 600 ሚሊየን ችግኝ የመትከል ዕቅድ እንዲሳካ የተለያዩ ክልሎች ዝግጅት ማድረጋቸውን ገለጹ። የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአካባቢ ጥበቃና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት…

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ ቡድን በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የልማት ስራዎችን እየጎበኘ ነው፡፡ በዞኑ በክላስተር የለማ ሰብል፣ በሰው ሰራሽ ዘዴ የእንሰሳት ማዳቀል ስራ፣ በማያ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች…

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በድሬዳዋ በእሳት አደጋ ምክንያት የተጎዱ ወገኖችን ለማቋቋም 6 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በድሬዳዋ አሸዋ ገበያ በቅርቡ በደረሰ የእሳት አደጋ ምክንያት የተጎዱ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም የ6 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የእሳት አደጋው ባደረሰው ጉዳት…

አቶ መላኩ አለበል ከሩስያ አምራቾች እና ዘርፍ ማህበራት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ከሩስያ አምራቾች እና ዘርፍ ማህበራት ጋር ተወያዩ፡፡ በውይይታቸውም በግብዓት አቅርቦት ፣ በወጪ ንግድ እና በጆይንት ቬንቸር አብሮ መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከራቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ…

ሚኒስቴሩ በህፃን ሄቨን ላይ በተፈፀመው ወንጀል በተሰጠው  ውሳኔ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር  እንደሚሰራ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በህፃን ሄቨን ላይ በተፈፀመው ዘግናኝ የሆነ ኢ ሰብአዊ ወንጀል የተሰጠው ዉሳኔ አስመልክቶ ይግባኝ ለመጠየቅ የሚኬድበት አግባብ ባለመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር  እንደሚሰራ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የህፃናትን መብት…