Fana: At a Speed of Life!
Browsing Tag

የተመረጡ

አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር አስተዋጽዖ ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ፡፡ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ በድምቀት ተከብሯል፡፡ ይህን ተከትሎም…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2017 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ ሙሉ መልዕክት

የተከበርከው የኦሮሞ ሕዝብ ሆይ እንኳን አስቸጋሪውን የክረምት ወቅት አልፈህ ለብሩሁ ብራ ተሸጋገርክ! ኢሬቻ ዕርቅ ነው፤ ፈጣሪ ደግሞ ዕርቅ ይወዳል። የተጣሉ ሰዎች ቂም ይዘው ለኢሬቻ ወደ መልካ አብረው አይወርዱም። ኢሬቻ መትረፍረፍ ነው! ኢሬቻ ምስጋና ነው! ኢሬቻ ልምላሜ ነው! ለምለም…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የብሪክስ የሚኒስትሮች ቅንጅት ኮሚቴ 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ የብሪክስ የሚኒስትሮች ቅንጅት ኮሚቴ ሦስተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በስብሰባው የኢትዮጵያ የብሪክስ ተሳትፎ ስትራቴጂ፣ የከፍተኛ ባለሞያዎች ኮሚቴ ያካሄደውን የኢትዮጵያ የዓመቱ የብሪክስ ተሳትፎ ግምገማ፣ ኢትዮጵያ…

ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የፌዴራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የብሔራዊ…

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸምን ተከትሎ በባንኮች ያለው የውጭ ምንዛሬ ክምችት በ80 በመቶ ጨምሯል ተባለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 207 (ኤፍ ቢ ሲ) የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸምን ተከትሎ በባንኮች ያለው የውጭ ምንዛሬ ክምችት በ80 በመቶ ጨምሯል ሲሉ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ተናገሩ፡፡ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አፈጻጸም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት…

በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ በመደረጉ በተያዘው የ2017 በጀት ዓመትም ኢትዮጵያ ባለሁለት…

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራው የተሻለ አፈጻጸም አስመዝግቧል – አቶ አሕመድ ሽዴ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሁለት ወራት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ገለጹ። የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አፈጻጸም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በዛሬው እለት ተገምግሟል፡፡…

ለ5 ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች የሥራ ፈቃድ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአምስት ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች የሥራ ፈቃድ መስጠቱን አስታወቀ፡፡ ባንኩ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎትና ተደራሽነትን ለማስፋፋትና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማዳበር አሁን በሥራ ላይ ካሉት ከባንክ ጋር…

ወደ ሀገራቸው መመለስ የሚፈልጉ በሊባኖስ የሚገኙ ዜጎች ምዝገባ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሊባኖስ በተከሰተው ውጥረት ምክንያት ኢትዮጵያውያን ጉዳት እንዳይደርስባቸው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ምዝገባ እንዲያከናውኑ ጥሪ ቀረበ፡፡ በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስል ጄነራል ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ÷ በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት…

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 5 አዳዲስ ዓለም አቀፍ የበረራ መዳረሻዎች ይኖሩኛል አለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተያዘው በጀት ዓመት አምስት አዳዲስ ዓለም አቀፍ የበረራ መዳረሻዎች እንደሚኖሩት አስታወቀ፡፡ አየር መንገዱ በየዓመቱ መዳረሻዎችን በማስፋትና የአውሮፕላኖችን ቁጥር በመጨመር ዓለም አቀፍ አገልግሎቱን እያጠናከረ መሆኑን…