Fana: At a Speed of Life!

መንግስት በወሰደው ሕግ የማስከበር ስራ በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ 5 ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት በወሰደው ሕግ የማስከበር ስራ በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀርበዋል። በአመራሮች ላይ ጥቃት ለመፈፀም እና ግድያን ለማስቀጠል ፣ ሕገ መንግስቱንና ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ…

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ በክልሉ መልሶ ግንባታ ዕቅድ ላይ መከረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡ ካቢኔው በስብሰባው የክልሉን መልሶ ግንባታ አስመልክቶ የተዘጋጀ ዕቅድ ላይ መምከሩን የክልሉ ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡ ከዚህ…

በመተከል ዞን ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪን ተቀብለው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ በመቀበል ወደ ቀደመ ሕይወታቸው ተመልሰዋል፡፡   ታጣቂዎቹ በጦርነትና ግጭት ከመጠፋፋት ውጭ ምንም አይነት መፍትሄ አለመኖሩን በመረዳት መንግስት ያቀረበውን…

በሲዳማ ክልል በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን የመለየት ስራ እየተከናወነ ነው 

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ የክልሉን ፀረ ሙስና ኮሚቴ የስራ እንቅስቃሴን ገምግመዋል፡፡ በግምገማው ወቅት ከመቶ በላይ ጥቆማዎች መቅረባቸውን የፀረ ሙስና ኮሚቴው  በሪፖርቱ አመላክቷል፡፡ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረትም በቂ…

ሻሸመኔ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መመለሱን አረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሻሸመኔ ከተማ የአዲስ አበባ ከተማን ሽንፈት ተከትሎ ከ15 የውድድር ዘመናት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መመለሱን አረጋግጧል፡፡ ሻሸመኔ ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ በሀገሪቱ ትልቁ ሊግ ተሳትፎ ያደረገው በ2000 ሚድሮክ ሚሌኒየም ፕሪሚየር ሊግ ላይ…

ናይጄሪያ የኢትዮጵያን የስንዴ ምርታማነት ልምድ መጋራት እንደምትፈልግ ገለጸች

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ናይጄሪያ የኢትዮጵያን የስንዴ ምርታማነት ልምድ መጋራት እንደምትፈልግ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት ካሺም ሼቲማ ገልጸዋል። በናይጄሪያ አዲሱ ተመራጭ ምክትል ፕሬዚዳንት ካሺም ሼቲማ የተመራው ከፍተኛ ልዑክ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን…

አቶ ደመቀ ከቱርክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከቱርክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ቡራክ አክሰፐር ጋር ተወያይተዋል፡፡   በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና ቱርክ መካከል ባለው የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን…

እየጣለ ያለው የበልግ ዝናብ በቀጣዩ ግንቦት ወርም ተጠናክሮ ይቀጥላል- ኢንስቲትዩቱ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) እየጣለ ያለው የበልግ ዝናብ በቀጣዩ የግንቦት ወርም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል። በአንዳድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከባድ ዝናብ የሚያስገኙ የሜቲዎሮሎጂ ክስተቶች ስለሚኖሩ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ…

የግብርና ሚኒስቴር ከመከላከያ ሚኒስቴር ጋር “በምግብ ሉዓላዊነት” ላይ እየሠራ መሆኑ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ሚኒስቴር ከኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር ጋር ከብሔራዊ ሉዓላዊነት ጎን ለጎን “በምግብ ሉዓላዊነት” ላይ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የግብርና ሚኒስቴር ከናይጄሪያ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ለተውጣጡ የሰራዊቱ ልዑካን ተሞክሮውን አካፍሏል።…

መንግስት ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን እየሠራ ነው – አቶ ደመቀ መኮንን

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን እየሠራ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በድጋሚ አረጋገጡ፡፡ አቶ ደመቀ መኮንን ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ ጋር…