Fana: At a Speed of Life!

ለ12ኛ ክፍል ፈተና የሚውሉ 450 ሺህ ታብሌቶች እስከ ታህሳስ መጨረሻ ወደ ሃገር ውስጥ እንደሚገቡ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ12ኛ ክፍል ፈተና የሚውሉ 450 ሺህ ታብሌቶች እስከ ታህሳስ ወር መጨረሻ ድረስ ከውጭ እንደሚገቡ ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ። በኦንላይን የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና እስከ ጥር መጨረሻ ድረስ ለመስጠት እቅድ መያዙን ሚኒስቴሩ…

በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀዋሳ ከተማን 4 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀዋሳ ከተማን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ። የቅዱስ ጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች ሮቢ ንግላንዴ በ33ኛው ደቂቃ ፣ ጌታነህ ከበደ በፍጹም ቅጣት ምትና በጨዋታ በ39ኛ እና 43ኛው ደቂቃዎች…

የመተከልን የጸጥታ ችግር ለመፍታት የሚያግዝ ህዝባዊ ውይይት በአሶሳ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከልን የጸጥታ ችግር ለመፍታት የሚያግዝ ህዝባዊ ውይይት ዛሬ በአሶሳ ከተማ ተጀምሯል። በውይይት መድረኩ ከክልሉ የተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። ውይይቱ የሀገር አቀፉ የማህበረሰብ…

አትሌት ወንድወሰን ከተማና እዮብ ኃብተስላሴ አበረታች ቅመሞች በመጠቀማቸው ከውድድር ታገዱ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የስፖርት አበረታች ቅመሞችን (ዶፒንግ) በመጠቀም የህግ ጥሰት በፈፀሙ አትሌቶች ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ፡፡ አትሌት ወንድወሰን ከተማ ማሞ እና አትሌት እዮብ ኃብተስላሴ ጎሳ የስፖርት አበረታች ቅመሞች (ዶፒንግ) በመጠቀም ተጠርጥረው ጊዜያዊ…

የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል በሠላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የፀጥታ አካላት አስታወቁ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14፣ 2013(ኤፍቢሲ) ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል በሠላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የምስራቅ ኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት አስታወቁ፡፡ የሀረሪ ክልል፣ የድሬዳዋ አስተዳደር፣ የምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች የፖሊስ ኮሚሽኖችና…

በደቡብ ክልል ከዚህ ቀደም በተፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች ተሳትፎ ያደረጉ 711 አመራሮች ከሀላፊነት ተነስተዋል

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል ከዚህ ቀደም በተፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች ተሳትፎ ያደረጉ 711 አመራሮች ከሀላፊነት መነሳታቸውን የደቡብ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ሰናይት ሰለሞን አስታወቁ፡፡ ሃላፊዋ በክልሉ የተካሄደውን የመንግስትና…

አስተዳደሩ በአማራ ክልል ለተፈናቀሉ ዜጎች 3 ሺህ ኩንታል የምግብ እህል ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በህግ ማስከበር ዘመቻው ለተፈናቀሉ የአማራ ክልል ዜጎች 3 ሺህ ኩንታል የምግብ እህል ድጋፍ አደረገ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሠለሞን ፍስሀ እንደገለፁት…

የጋዜጠኛ እና አርቲስት ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 14፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የጋዜጠኛ፣ አርቲስት እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ዕድገት ውስጥ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተው ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርአተ ቀብር ተፈጸመ፡፡ ኢብራሂም ሀጂ አሊ ካለፈው ክረምት ጀምሮ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ የህክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቶ ትናንት…

እስራዔል በሁለት ዓመት ውስጥ ለአራተኛ ጊዜ ምርጫ ልታካሂድ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) እስራዔል በሁለት ዓመት ውስጥ ለአራተኛ ጊዜ ወደ ጠቅላላ ምርጫ ልታመራ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ምርጫው የሚካሄደው መንግስቱን የመሰረቱት ሁለቱ ፓርቲዎች በበጀት ጉዳይ ላይ ባለመስማማታቸው ነው ተብሏል፡፡ መራጮች ከ12 ወራት በኋላ በመጋቢት ወር…

በየዕለቱ ከ300 በላይ የኮቪድ ታማሚዎች ወደ ጽኑ ህክምና እንደሚገቡ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በየቀኑ ኮቪድ-19 ከሚገኝባቸው ሰዎች ውስጥ ከ300 በላይ የሚሆኑት ጽኑ ህክምና እንደሚያስፈልጋቸው እና ከእነዚህ ውስጥ እስከ 50 የሚደርሱት የመተንፈሻ አካልን የሚረዳ ማሽን የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የጤና ሚኒስትር…