Fana: At a Speed of Life!

የፀጥታ ኃይሎች ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በታች የሆነን ገንዘብ በህገ ወጥነት መያዝ እንደሌለባቸው ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፀጥታ ኃይሎች ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በታች የሆነን ገንዘብ በህገ ወጥነት መያዝ እንደሌለባቸው ተገለፀ። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና የብሄራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ በዛሬው እለት አዲሱን የብር ኖት ለውጥ ተከትሎ መግለጫ…

የፍቺ ጥያቄ በ300 ፐርሰንት መጨመሩ እየተነገረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፍቺ ጥያቄ በ300 ፐርሰንት መጨመሩ ዘጋርድያን ትናንት ማምሻውን ዘግቧል፡፡ የፍቺ ጥያቄው በዚህ መጠን ሊጨምር የቻለው የኮሮና ቫይረስ ባስከተለው መዘዝ መሆኑ ነው የተነገረው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከዚህ ቀደም ባልታየ መልኩ ሰዎች ስለ ስለሞት…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በጅማና ዳውሮ ጉብኝት አድርገዋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በጅማ  እና ዳውሮ ጉብኝት አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጅማ አባ ጅፋር አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በአባ ገዳዎች፣ በሀይማኖት አባቶች የሀገር ሽማግሌዎች እና የተለያዩ የህብረተሰብ…

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጎርፍ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች 29 ሚሊየን ብር የሚገመት በገንዘብ እና በአይነት ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 8 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጎርፍ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች 29 ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ በገንዘብ እና በአይነት ድጋፍ አደረገ። ድጋፉ ከተማ አስተዳደር በጀት፣ የብልጽግና ወጣቶች ሊግ፣ በጎፍቃደኞች እና አሚባራ ኃ.የ.ግ.ማ የተሰበሰበ…

የመስቀል በዓልን ምክንያት ያደረገ ጉዞ ማድረግ አይገባም – አቶ ርስቱ ይርዳው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የመስቀል በአልን ምክንያት ያደረገ ጉዞ ማድረግ እንደማይገባ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው ተናገሩ፡፡ ምክትል ርእስ መስተዳደሩ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ በክልሉ በደማቁ የሚከበረውን የመስቀል…

የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በመተከል ዞን የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ የተፈጠረውን ችግር…

የኦሮሚያ ክልል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በአፋር ክልል በጎርፍ የተጎዱ አካባቢዎችን በመጎብኘት ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል ርእስ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ቡድን በአፋር ክልል በጎርፍ የተጎዱ አካባቢዎችን በመጎብኘት ድጋፍ አደረገ። የአዋሽ ወንዝ በመሙላት በአፋር ክልል ባስከተለው ተጎርፍ አደጋ በርካቶችን…

የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን አስመልክቶ የአውሮፓ ሀገራትን አስጠነቀቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን አስመልክቶ የአውሮፓ ሀገራትን አስጠነቀቀ፡፡ ድርጅቱ በመላው አውሮፓ ሀገራት እየተመዘገበ ያለው በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እንደማንቂያ ደውል ሆኖ ሊያገለግሉ ይገባልም ነው ያለው፡፡ የአለም…

የኤፍ.ቢአ.ይ ኃላፊ ሩስያ አሜሪካ በቅርቡ በምታካሂደው ምርጫ ላይ ጣልቃ ለመግባት እየሞከረች ነው ሲሉ አስጠነቀቁ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካ ፌደራል ምርመራ ቢሮ (ኤፍ.ቢአ.ይ) ኃላፊ  ክርስቶፈር ሬይ ሩስያ ዋሽንግተን በቅርቡ በምታካሂደው ምርጫ ላይ ጣልቃ ለመግባት እየሞከረች ነው ሲሉ አስጠነቀቁ፡፡ አሜሪካ በቅርቡ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫዋን ለማድረግ እየተሰናዳች ትገኛለች፡፡…

መሃመድ ሁሴን ሮብሌ የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሶማሊያ ፕሬዚዳንት መሀመድ አብዱላሂ ፋርማጆ መሃመድ ሁሴን ሮብሌን አዲሱ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርገው መረጡ። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር መሃመድ ሁሴን ሮብሌን የተመረጡት ባላቸው ዕውቀት፣ ልምድና ችሎታቸው መሆኑን ፕሬዚዳንት…