Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ለእስልምና እምነት ተከታዮች ለረመዳን ጾም የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለእስልምና እምነት ተከታዮች ለረመዳን ጾም የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።   “ታላቁ የረመዳን ወር የተቀደሰ የፆም፣ የፀሎትና የመንፈሳዊነት ወር ነው” ያሉት ጠቅላይ…

ጠ/ሚ ዐቢይ ከአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ አባላት፣ ከሀገራት መሪዎችና ከ20 በላይ አፍሪካውያን የንግድ ሰዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ አባላት፣ ከሀገራት መሪዎችና ከ20 በላይ አፍሪካውያን የንግድ ሰዎች ጋር ተወያዩ። በውይይታቸውም የግሉ ዘርፍ የኮቪድ19ን ቀውስ ከመቋቋም አንጻር ያለውን ሚናን…

በኮቪድ 19 ስጋት አንዳንድ የጤና ተቋማት መደበኛ የህክምና አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮናቫይረስ (ኮቪድ 19) ስጋት አንዳንድ የጤና ተቋማት መደበኛ የህክምና አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። በዚህም ሳቢያ እናቶች በቤት ውስጥ እንዲወልዱ ሆኗል፤ በህክምና ሊድኑ በሚችሉ በሽታዎች የሰው ህይወት እያለፈ…

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ በለይቶ ማቆያ የሚገኙ ዜጎችን አያያዝ መጎብኘት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ በለይቶ ማቆያ የሚገኙ ዜጎችን አያያዝ መጎብኘት ጀመረ። መርማሪ ቦርድ በለይቶ ማቆያ የሚገኙ ዜጎችን በዛሬው እለት መጎብኘት መጀመሩን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታውቋል።…

በለይቶ ማቆያ የሚገኙ ዜጎች አያያዝ ሊገመገም ነው

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ በለይቶ ማቆያ የሚገኙ ዜጎችን አያያዝ ከነገ ጀምሮ ሊገመግም ነው። በዚህም መንግስት ለዜጎች የሰጠው ትኩረት እና ዜጎች ያሉበት አጠቃላይ ሁኔታ እንዲሁም ከሰብዓዊ መብት አንጻር ምልከታ እንደሚደረግ መርማሪ…

1441ኛው የረመዳን ፆም አርብ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ታላቅ ቦታ ያለው የረመዳን ፆም የፊታችን አርብ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዬች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዬች ጠቅላይ ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነት ሃላፈ ዑስማን አደም ለፋና ብሮድካስቲንግ…

ከጅቡቲ ወደ አፋር ክልል የገቡ 336 ዜጎች በአስገዳጅ የለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ አቅጣጫዎች ከጅቡቲ ወደ አፋር ክልል የገቡ 336 ዜጎች በአስገዳጅ የለይቶ ማቆያ እንዲገቡ መደረጉን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ያሲን ሀቢብ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ከጅቡቲ ወደ ክልሉ…

የንግድ ተግባሩን ባስተጓጎሉ 25 ሺህ 68 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ የንግድ ተግባሩን ባስተጓጎሉ 25 ሺህ 68 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በሰጡት መግለጫ በንግድ ተቋማቱ ላይ ከማስጠንቀቂያ…