Fana: At a Speed of Life!

የኮሮና ቫይረስ ህሙማንን ለሚረዱ የጤና ባለሙያዎች 645 መኖሪያ ቤቶች ተዘጋጁ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ለኮሮና ቫይረስ ህመምተኞች እርዳታ የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎች የሚያርፉባቸው ከ645 በላይ የመኖሪያ ቤቶች መዘጋጀታቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ። ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት ይህን ወረርሽኝ በመቆጣጠርና ምላሽ በመስጠት…

በሀገር አቀፍ ደረጃ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ሳይኖር የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ ከ25 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀገር አቀፍ ደረጃ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ሳይኖር የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ ከ25 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ። የኮሮና ቫይረስ ከተከሰተ በኋላ ማህበረሰቡ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ያለምንም የዋጋ ጭማሪ እንዲያገኝ ብሔራዊ የገበያ ማረጋጋት…

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ18ኛ አስቸኳይ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 18ኛ አስቸኳይ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።   የምክር ቤቱ ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦   1. ምክር ቤቱ በመጀመሪያ የተወያየው…

የሚኒስቴሮች ምክር ቤት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደነገገ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 93 በተደነገገው መሠረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደነገገ። ኮቪድ-19 በዓለም አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚ…

የጅማ ዩኒቨርሲቲ 200 አልጋዎቹ ያለት የኮቪድ-19 የህክምና ማዕከል አዘጋጀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የጅማ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ማዕከል 200 አልጋዎቹ ያለት የኮቪድ-19/ኮሮና ቫይረስ/ የህክምና ማዕከል ማዘጋጀቱን አስታወቀ። ማዕከሉ በቫይረሱ የተጠረጠሩ 3 ሺ ሰዎች የሚስተናገዱበት የለይቶ ማቆያ ስፍራ እንዳለውም ተገልጿል። 300 የህክምና…

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 225 ሰዎች መካከል 3 ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር አስታወቀ። በዚህም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 55 ከፍ ብሏል።…

የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባውን እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባውን እያካሄደ ነው።   በዛሬው እለት የተጀመረው የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባ የኮሮና ወረርሽኝና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መክሮ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ…

በከተሞች የምግብ ዋስትና ፕሮግራም የመጀመሪያዎቹ ተጠቃሚዎች የሶስት ወር ቅድሚያ ክፍያ እንዲከፈላቸው ተወሰነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴራል የከተሞቸ ልማታዊ ሴፍቲ ኔት ፕሮጀክት ስቲሪንግ ኮሚቴ ከኮሮና ቫይረስ መከሰት ጋር በተያያዘ በዝቅተኛ ደረጃ ያሉ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ውሳኔዎችን አሳለፈ፡፡ ኮሚቴው ባካሄደው ስብሰባ ከከተሞች የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ…

የኮሮና ቫይረስ የወቅቱ ከፍተኛ ችግር በመሆኑ ቀዳሚ ትኩረት ሆኖ መከላከሉ ላይ መሰራት አለበት – የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ቫይረስ በዜጎች ላይ ያንዣበበ የወቅቱ ከፍተኛ ችግር በመሆኑ ቀዳሚ ትኩረት ሆኖ ለመከላከሉ መሰራት እንዳለበት የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ። ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቹ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ባደረጉበት ወቅት ከሁሉ…