Fana: At a Speed of Life!

አሜሪካ 12 ሺህ ወታደሮቿን ከጀርመን ልታስወጣ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ 12 ሺህ ወታደሮቿን ከጀርመን ልታስወጣ መሆኑን አስታወቀች፡፡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን በጀርመን ከሚገኘው 36 ሺህ ሰራዊቷ ውስጥ 1/3 የመቀነስ እቅድ እንዳላቸው ባለፈው ወር ተናግረው ነበር፡፡ ይህን ተከትሎም 12 ሺህ…

610 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ14 ሰዎች ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰአታት ለ7 ሺህ 760 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 610 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የ14 ሰዎች ህይወት በቫይረሱ ሳቢያ ማለፉንም በፌስ ቡክ ገጻቸው…

መርማሪ ፖሊስ በአቶ ጃዋር መሃመድ ቤት በግለሰብ እጅ የማይገኙ ሳተላይቶችና ከውጭ በድብቅ የገቡ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማግኘቱን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴራል መርማሪ ፖሊስ በአቶ ጃዋር መሃመድ ቤት በድጋሚ ባደረገው ፍተሻ በግለሰብ እጅ የማይገኙ ሳተላይቶችና ከውጭ በድብቅ የገቡ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ማግኘቱን ገለጸ። መርማሪ ፖሊስ ሃምሌ 9 ቀን 2012 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ በተሰጠው የ13…

የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮችና የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አባላት ችግኝ ተከሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ዑመርን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች የችግኝ ተከላ አካሂደዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ የሀገር አቀፍ አረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም አካል አንድ የሆነው በክልሉ በአንድ ጀንበር ሚሊዮን…

የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የሰላም ሚኒስቴር በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የሰላም ሚኒስቴር በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አደም ፋራህ የጋራ መፍትሔ የሚሹ ጉዳዮች ወደ ሁለቱም ተቋማት እንደሚመጡ አውስተዋል፡፡ ከዚህ አንጻር…

በህግ የተጀመረው ስራ በህግ የሚጨረስ መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው- ጠ/ዐቃቤ ህግ ወ/ሮ አዳነች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የህግ የበላይነት ማክበር፣ ማስከበር እና ፍትህን ማስፈን የህልውናችን መሰረት ነው ሲሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ህግ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ። የህግ የበላይነት እና ፍትህ እንዲሰፍን ዘርፈ ብዙ ስራ እና ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ በፌስቡክ ገፃቸው…

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 12 ሰዓታት 327 ሚሊየን 399 ሺህ 570 ችግኞች ተተክሏል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል በአንድ ጀንበር ማለትም ከጠዋቱ 12 እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ 327 ሚሊየን 399 ሺህ 570 ችግኞች ተተክሏል፡፡ በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የተለያዩ…

በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ በተፈፀመ ጥቃት የ13 ዜጎች ሕይወት ማለፉን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ጉባ ወረዳ በተፈፀመ ጥቃት የ13 ዜጎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ሠላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ ከሀገር ውጭና ከውስጥ ተልዕኮ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር ባካሄዱት ውይይት ላይ የተነሱ ጉዳዮች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጠዋት ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡ ውይይቱ ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ከተካሄዱ የምክክር መድረኮች የቀጠለ መሆኑ እና የዛሬው ውይይት በሁለት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ…

ኢትዮጵያ እና አልጀሪያ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ እና አልጀሪያ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ። በአልጀሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን የተሾሙት ነቢያት ጌታቸው በኢትዮጵያ የአልጀሪያ አምሳደር እና የሀገሪቱ የአፍሪካ ህብረት ቋማ ተጠሪ ከሆኑት ኤልሃምዲ ሳላህ ጋር…