Fana: At a Speed of Life!

የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ውይይት ያለስምምነት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአዲስ አበባ ሲያካሂዱት የቆዩት የሶስትዮሽ ውይይት ያለስምምነት ተጠናቋል። የሶስትዮሽ ውይይቱ መጠናቀቁን ተከትሎ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ መግለጫ…

በኢትዮጵያ የታየው ለውጥ በጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እስኪተካ ሁሉም የፖለቲካ ኃይል በሰከነ መንገድ ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የታየው ለውጥ በጠንካራ ዴሞክራሲያዊ  ስርዓት እስኪተካ ሁሉም የፖለቲካ ሃይላት በተደራጀ እና በሰከነ መንገድ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ አንጋፋዎች ፖለቲከኞች ዶክተር ዲማ ነግዎ እና የኢህአፓ ፓርቲ መሪ ቆንጂት ብርሃኑ ተናገሩ። ፖለቲከኞች…

ማራቶን ሞተርስ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን መገጣጠም ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ማራቶን ሞተርስ ኢንጂነሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በመጭዎቹ 3 ወራት መገጣጠም ሊጀምር ነው። ኩባንያው በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የሃዩንዳይ ምርቶችን በመጭዎቹ ሶስት ወራት…

በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ በዛሬው እለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት አለፈ። ከምዕራብ አባያ ወረዳ ወደ አርባምንጭ ከተማ ሲጓዝ የነበረ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ/ሚኒ ባስ ተሽከርካሪ መኪና ላይ ዛሬ ጥዋት 2:30 አከባቢ…

አማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር የሼር ሽያጭ ጊዜውን እስከ የካቲት 30 ድረስ አራዘመ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስረታ ላይ የሚገኘው አማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር የሼር ሽያጭ ጊዜውን እስከ የካቲት 30 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን አስታወቀ። ባንኩ የአክሲዮን ሽያጩን በውጭ ሃገር የሚኖሩ ዜጎች እና ባለሃብቱ የመግዛት ፍላጎት ማሳየታቸውን ተከትሎ…

በከተሞች የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት የቅንጅት ስራ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በከተሞች የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት የቅንጅት ስራ አስፈላጊ መሆኑን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታወቀ። የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ህንፃ ኮሌጅ አመራሮች ጋር በከተሞች የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የኢኳቶሪያል ጊኒን የክብር ኒሻን ተሸለሙ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢኳቶሪያል ጊኒን የክብር ኒሻን ተሸለሙ። ሽልማቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገር ውስጥ እና ሰላምን ከማስፈን አንጻር በአፍሪካ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የተበረከተ መሆኑም ታውቋል። ከፕሬዚዳንት ቴዎዶር…

ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ የሚከተሉ ሰዎች ከበሽታ ነጻ የሆኑ ረጅም አመታትን ያሳልፋሉ – ጥናት

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ የሚከተሉ ሰዎች ከበሽታ ነጻ የሆኑ ረጅም አመታትን እንደሚያሳልፉ አንድ ጥናት አመላከተ። በአሜሪካ ከ20 ዓመታት በላይ በተካሄደው ጥናት 111 ሺህ ሰዎች ላይ የጤና ክትትል ተደርጓል። በተደረገው ጥናት የተሳተፉ ሰዎች…

በአዋሽ ተፋሰስ ቆላማ አካባቢዎች የቆላ ስንዴ ልማት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዋሽ ተፋሰስ ቆላማ አካባቢዎች የቆላ ስንዴ ልማት እየተካሄደ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። በተፋሰሱ ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ የመስኖ የቆላ ስንዴ ልማት እየተካሄደ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 4 ሺህ ሄክታር የሚሆነው መሬት…