Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ቢሳው አቀና

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ ቢሳው ጋር ለሚያደርገው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ መዲናዋ ቢሳው ተጉዟል። 23 ተጫዋቾችን ያካተተው ልዑካን ቡድኑ ከአዲስ አበባ በቶጎ (ሎሜ) አድርጎ ቢሳው ከተማ ዛሬ ምሽት ላይ እንደሚደርስ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ ብሔራዊ ቡድኑ ለዓለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታ ወደ ጊኒ ቢሳው ከማምራቱ አስቀድሞ የመጨረሻ የሀገር ቤት ልምምዱን ትናንት በአዲስ አበባ ስታዲየም ማከናወኑ ተገልጿል።
Read More...

በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ለሜቻ ግርማ የዓመቱን የዓለም ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስዊድን በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት አትሌት ለሜቻ ግርማ የዓመቱን የዓለም ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸነፈ፡፡ በዚህም መሠረት በ3 ሺህ ሜትር መሠናክል የወንዶች ውድድር አትሌት ለሜቻ ግርማ 8 ደቂቃ ከ1 ሰከንድ ከ63 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሲያሸንፍ÷ ሳሙኤል…

በማድሪድ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ጥሩነሽ ዲባባ 3ኛ ስትወጣ ዳዊት ወልዴ በቀደሚነት አጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ማድሪድ በተካሄደው የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በሴቶች አንጋፋዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። በወንዶች ደግሞ ዳዊት ወልዴ በቀዳሚነት አጠናቋል፡፡ ጥሩነሽ 10 ኪሎ ሜትሩን በ30 ደቂቃ ከ03 ሴኮንድ በመጨረስ ነው 3ኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው፡፡ በወንዶች የ10 ኪሎ ሜትር…

የሻምፒዮንስ ሊጉ የፍጻሜ ጨዋታ ነገ ምሽት በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023/24 አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ነገ ምሽት በእንግሊዙ ዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ሊደረግ ቀጠሮ በተያዘለት ታላቁ የፍጻሜ ጨዋታ የአውሮፓ ሻምፒዮንሰ ሊግ ንጉሶቹ ሪያል ማድሪድ እና የጀርመኑ ክለብ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ የባለ ትልቁ ጆሮ ዋንጫ ለማንሳት ይፋለማሉ፡፡ በጨዋታው ሎስ…

ሐጎስ ገብረህይወት በ5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ሐጎስ ገብረህይወት በዳይመንድ ሊግ የ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ውድድር አሸንፏል፡፡ በውድድሩ 12፡36፡73 ሰዓት በመግባት ሲያሸንፍ ፥ በ5ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ሪከርድ ለመስበር በሁለት ሰከንድ ዘግይቶ መግባቱ ተገልጿል፡፡ አትሌቱ በተሳተፈበት በዚህ ውድድርም በታሪክ የምንጊዜም ሁለተኛውን ፈጣን…

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ የትጥቅ ብራንድ ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቱርክ ከሚገኝ የትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር በመተባበር “ሀገሬ” የተሰኘ የራሱን ብራንድ ማስተዋወቁን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራ እንደገለጹት÷ ፌዴሬሽኑ ከተቋሙ ጋር ያደረገው የመግዛት እና የመሸጥ ስምምነት የጊዜ ገደብ የለውም፡፡ ፌዴሬሽኑ ያስተዋወቀው የትጥቅ ብራንድ…

ቪንሴንት ኮምፓኒ የባየር ሙኒክ አሰልጣኝ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ቤልጂየማዊውን ቪንሴንት ኮምፓኒን በአሰልጣኝነት መሾሙን አስታውቋል፡፡ ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን በኃላፊነት የተረከበው የቀድሞው የቡድኑ አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል መሰናበቱን ተከትሎ ነው፡፡ በዚህም አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ ባየር ሙኒክን ለሦስት የውድድር ዓመታት ለማሰልጠን እስከ 2027 የሚያቆየውን…