ስፓርት
በቫሌንሺያ ማራቶን አትሌት ደረሳ ገለታ 2ኛ ደረጃን ያዘ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ቫሌንሺያ በተካሄደው የወንዶች ማራቶን ውድድር አትሌት ደረሳ ገለታ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ፡፡
ኬንያውዩ አትሌት ሴባስቲያን ሳዌ ውድድሩን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ÷ ሌላኛው ኬንያውይ አትሌት ዳኒኤል ማቴኮ ሦስተኛ ሆኗል፡፡
እንዲሁም አትሌት ጪምዴሳ ደበሌ 6ኛ እና የአምናው የውድድሩ አሸናፊ አትሌት ሲሳይ ለማ 10ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል፡፡
በዘንድሮው ውድድር ላይ የሦስት ጊዜ ኦሊምፒክ ባለ ድሉ አትሌት ቀነኒሳ በቀለም ተሳተፏል፡፡
Read More...
በወዳጅነት ዐደባባይ ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ በወዳጅነት ዐደባባይ ከሁሉም የመዲናዋ ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሂዷል፡፡
የአካል ብቃት እንቅስቃሴው የተካሄደው÷ “ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል የነገን ስብዕና ይገነባል” በሚል መሪ ሐሳብ…
ሊቨርፑል ከማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ13ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብሮች ሲቀጥሉ ምሽት 1 ሠዓት ላይ ሊቨርፑል በአንፊልድ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል፡፡
ሊጉን በ31 ነጥቦች እየመራ የሚገኘው የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ውኃ ሰማያዊዮቹን ያሸንፋል የሚሉ የቅድመ-ጨዋታ አስተያየቶችም ተበራክተዋል፡፡
በሌላ…
በለንደን ደርቢ አርሰናል ዌስትሃም ዩናይትድን 5 ለ 2 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ አምስት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ወደ ለንደን ስታዲየም በማቅናት ዌስትሃም ዩናይትድን የገጠመው አርሰናል 5 ለ 2 በሆነ ሰፊ ልዩነት አሸንፏል፡፡
የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ጋብሬል ማጋሌሽ፣ ትሮሳርድ፣ ኦዴጋርድ ፣ ሃቨርትዝ እና ሳካ…
በለንደን ደርቢ ዌስትሃም ዩናይትድ ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሐ ግብሮች ዛሬ ሲካሄዱ በለንደን ደርቢ ዌስትሃም ዩናይትድ ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ መድፈኞቹ ወደ ለንደን ስታዲየም በማቅናት ዌስታም ዩናይትድን ይገጥማሉ፡፡
በአርሰናል በኩል ብራዚላዊው ተከላካይ ጋብረኤል ማጋሌሽ በጉዳት…
መቻል አርባምንጭ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳንምት መርሐ ግብር መቻል አርባምንጭ ከተማን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ መቻል ሽመልስ በቀለ ሁለት እንዲሁም አብዱልከሪም ወርቁ አንድ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
አርባምንጭ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችውን…
አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳንምት አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
በድሬዳዋ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ አዳማ ከተማ ስንታየሁ መንግስቱ ባስቆጠራቸው ሁለት ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
ኢትዮጵያ ቡና ከሽንፈት ያላዳነውን ብቸኛ ግብ…