Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ወላይታ ድቻና ሲዳማ ቡና አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 15ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ እና ሲዳማ ቡና አቻ ተለያይተዋል፡፡ ቡድኖቹ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ያደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል መቐለ 70 እንደርታ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ምሽት12 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ፡፡
Read More...

አርሰናል እና አስቶንቪላ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኤምሬትስ ስታዲየም የተደረገው የአርሰናል እና አስቶንቪላ ጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡ ይህን ጨዋታ አርሰናል ማርቲኔሊ በ35ኛው እና ሀቨርትዝ በ55ኛው ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሲመራ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ ቴሌማንስ በ60ኛው እንዲሁም ዋትኪንስ በ68ኛው ግብ ማስቆጠራቸው ተከትሎ የመድፈኞቹ መሪነት ከ13…

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና አርባ ምንጭ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 15ኛ ሣምንት መርሐ-ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ በአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ÷ የቅዱስ ጊዮርጊስን ግቦች ኢስማኤል አብዱል ጋንዩ (በራስ ላይ) እና ፍፁም ጥላሁን (በፍፁም ቅጣት ምት) አስቆጥረዋል፡፡ ሁለቱም ግቦች የተቆጠሩት…

ሊቨርፑል ተጋጣሚውን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ22ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በርካታ ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ በዚሁ መሠረት ከሦስቱ ጨዋታዎች ቀደም ብሎ በተደረገው መርሐ-ግብር በሜዳው በርንማውዝን ያስተናገደው ኒውካስል ዩናይትድ 4 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል፡፡ እንዲሁም በተመሳሳይ ሠዓት በተደረጉት ጨዋታዎች ÷ ዌስትሃም ዩናይትድ በክሪስታል ፓላስ እና…

ኧርሊንግ ሃላንድ በማንቸስተር ሲቲ እስከ 2034 የሚያቆየውን ኮንትራት ፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማንቸስተር ሲቲው አጥቂ ኧርሊንግ ሃላንድ በቡድኑ እስከ 2034 የሚያቆየውን ውል መፈረሙ ተገለጸ። የ24 ዓመቱ ኖርዌያዊ አጥቂ ከቅርብ ጊዜ  ወዲህ የአቋም መውረድ ማሳየቱን ተከትሎ ቡድኑን ሊለቅ ይችላል የሚል ጭምጭምታ ሲሰማ እንደነበር ዘገባዎች ያመላክታሉ። ሃላንድ በፈረንጆቹ ሰኔ 2022…

ኦሊጎነር ሶልሻየር የቤሽክታሽ አሰልጣኝ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ ተጫዋች ኦሊጎነር ሶልሻየር የቤሺክታሽ እግር ኳስ ቡድን አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ። ሶልሻየር የቱርኩን እግር ኳስ ቡድን እስከ 2026 ለማሰልጠን መስማማቱን የተረጋገጡ የዝውውር መረጃዎችን የሚያወጣው ፋብሪዚዮ ሮማኖ በፌስ ቡክ ገፁ አስፍሯል። ኦሊጎነ ሶልሻየር በማንቸስተር ዩናይትድ ከሁለት ዓመት…

ድሬ ሀሪፍ ሀገር አቀፍ የብስክሌት ውድድር ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከታሕሣሥ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በድሬዳዋ ሲደረግ የቆየው ድሬ ሀሪፍ ሀገር አቀፍ የብስክሌት ውድድር የማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል። በመርሐ ግብሩ ከአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ትግራይ እና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ የተውጣጡ 36 የከፍተኛ ኮርስ ብስኪሌተኞች ተሳትፈዋል፡፡ 80 ኪሎ ሜተር በሸፈነው የፍጻሜ ውድድር ዐቢይ…