ስፓርት
ቼልሲ ከአሰልጣኙ ጋር ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ አሰልጣኝ ማውሪስዮ ፖቸቲኖን በጋራ ስምምነት ከአሰልጣኝነት አሰናበተ፡፡
የ52 ዓመቱ ፖቸቲኖን እንደ አውሮፕያኑ አቆጣጠር ሐምሌ 1 ቀን 2023 ነበር ቼልሲን ለማሰልጠን የሁለት ዓመት ኮንትራት የተፈራረሙት፡፡
ቼልሲ የዘንድሮውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በ6ኛ ደረጃ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
Read More...
ቶኒ ክሩስ ከዩሮ 2024 በኋላ ጫማ እንደሚሰቅል አስታውቋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሪያል ማድሪድ እና የጀርመኑ አማካኝ ቶኒ ክሩስ በቀጣይ ወር ሀገሩ ከምታስተናግደው ዩሮ 2024 መጠናቀቅ በኋላ ጫማ እንደሚሰቅል አስታውቋል፡፡
በፈረንጆቹ ጥር 4/1990 በምስራቅ ጀርመን የተወለደው ክሩስ የፕሮፌሽናል እግርኳስ ህይወቱን የጀመረው በባየር ሙኒክ ሲሆን ሶስት የቡንደስሊጋ እና ሶስት የጀርመን ጥሎ ማለፍ…
ማንቼስተር ሲቲ የ2023/24 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ማንቼስተር ሲቲ ብርቱ ፉክክር በታየበት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2023/24 የውድድር ዘመን ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
በዛሬው ዕለት ፍጻሜውን ባገኘው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሜዳው ዌስትሃምን ያስተናገደው ማንቼስተር ሲቲ 3 ለ1 ማሸነፉን ተከትሎ ነው ሻምፒዮንነቱን ያረጋገጠው፡፡
በዚህም 91 ነጥቦችን በመሰብሰብ ፕሪሚየር…
የ2023/24 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምሽቱን ፍጻሜውን ያገኛል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2023/24 የውድድር ዘመን ዛሬ በተመሳሳይ አመሻሽ 12:00 ላይ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይጠናቀቃል።
የሊጉ መሪ ማንቼስተር ሲቲ እና ተከታዩ አርሰናል ዋንጫውን የማሸነፍ ዕድል ይዘው በሜዳቸው ተጋጣሚዎቻቸውን ያስተናግዳሉ።
ማንቼስተር ሲቲዎች በኢቲሃድ ከዌስትሃም ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ በድል…
በፕሪሚየር ሊጉ አዳማ ከተማ ተጋጣሚውን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ25ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አዳማ ከተማ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 1 ረትቷል፡፡
በጨዋታውም መስዑድ መሐመድ እና ቢንያም አይተን ለአዳማ ከተማ እንዲሁም ደስታ ዮሐንስ ለሲዳማ ቡና ጎሎቹን ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል፡፡
እንዲሁም 12 ሠዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ ሻሸመኔ ከተማን ኢትዮጵያ ቡና 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡…
ኢትዮጵያ 3ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ስታሸንፍ የቡድኑ አባል የነበሩት ኃ/ማርያም መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ1954 ኢትዮጵያ ሦስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ስታሸንፍ የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋች የነበሩት ኃይለማርያም መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡
በቅፅል ስማቸው "ሻሾ" በሚል በስፖርት ቤተሰቡ በስፋት የሚታወቁት ኃይለማርያም መኮንን÷ ከ1940ዎቹ መጨረሻ እስከ 60ዎቹ መጀመሪያ በነበረው የተጫዋችነት ሕይወታቸው ለጥቅምት 23፣ ሸዋ…
በጃፓን የዓለም ፓራ-አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጃፓን እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ፓራ-አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በሻምፒዮናው በአራት የጉዳት ዘርፎች ከተሳተፉ አትሌቶች መካከል ትዕግስት ገዛኸኝ በ1 ሺህ 500 ሜትር (ቲ13 ቡድን) በቀዳሚነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች፡፡
አትሌት ትዕግስት ርቀቱን ያጠናቀቀችበት 4…