ስፓርት
ኢትዮጵያ መድን ስሑል ሽረን አሸንፏል
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ12ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ መድን ስሑል ሽረን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡
መሐመድ አበራ፣ ረመዳን የሱፍ እና መስፍን ዋሼ የኢትዮጵያ መድን ጎሎችን ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
የስሑል ሽረን ግብ ያስቆጠረው ደግሞ አሌክስ ኪታታ ነው፡፡
በአዳማ ሣይንስ እና ቴክኖሎጂ ስታዲየም እየተካሄደ የሚገኘው የዛሬ መርሐ-ግብር ሲቀጥል 12 ሠዓት ላይ መቻል ከሀድያ ሆሳዕና ይገናኛሉ፡፡
Read More...
አዳማ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ12ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አዳማ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 0 ረትቷል፡፡
በአዳማ ሣይንስ እና ቴክኖሎጂ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ÷ የአዳማ ከተማን ጎሎች አሜ መሐመድ፣ ነቢል ኑሪ እና ኤሊያስ ለገሠ አስቆጥረዋል፡፡
በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመቐለ 70…
ሊቨርፑል ታሪካዊ ተቀናቃኙ ማንቸስተር ዩናይትድን ዛሬ ይገጥማል
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር መሪው ሊቨርፑል 14ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ማንቸስተር ዩናይትድን ዛሬ ምሽት በሜዳው አንፊልድ ሮድ ያስተናግዳል፡፡
ሊጉ በፈረንጆቹ 1992/93 የውድድር ዓመት በአዲስ መልክ ከተዋቀረ ጀምሮ 65 ጊዜ ተገናኝተው ማንቸስተር ዩናይትዶች 29 ጊዜ ሲያሸንፉ በአንፃሩ…
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ክብረ ወሰን በመስበር አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ዳዊት ወልዴ እና አትሌት ሩቲ አጋ በ2025 የሺያሚን የማራቶን ሩጫ ውድድር ሪከርድ በመስበር አሸንፈዋል፡፡
በዢያሜን ማራቶን 2025 የወንዶች ሩጫ ውድድር አትሌት ዳዊት ወልዴ 2:06:06 በሆነ ሰዓት በመግባት ቀደም ሲል የተያዘውን ክብረ ወሰን በመስበር አሸንፏል፡፡
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ…
ባሕርዳር ከተማና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ12ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባሕርዳር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ባሕርዳር ከተማ ሙጂብ ቃሲም ባስቆጠራት ግብ እስከ ጨዋታው መጠናቀቂያ ድረስ መምራት ችሎ ነበር፡፡
ይሁን እንጂ አሕመድ ረሺድ 88ኛው ደቂቃ ላይ ኳስ…
ማንቼስተር ሲቲ በሰፊ የግብ ልዩነት ሲያሸንፍ ቼልሲ ነጥብ ጥሏል
አዲስ አበባ፣ ታህሣሥ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር ማንቼስተር ሲቲ ዌስትሃም ዩናይትድን 4 ለ 1 ሲያሸንፍ ቼልሲ ከክሪስታል ፓላስ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ለማንቼስተር ሲቲ የማሸነፊያ ግቦቹን ኩፋል በራሱ ግብ ላይ እንዲሁም ኧርሊንግ ሃላንድ (2) እና ፊል ፎደን ሲያስቆጥሩ÷…
የኢትዮጵያ ክለቦች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለተከታታይ አምስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ ክለቦች የአጭር፣ መካከለኛ፣ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ርምጃ እና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቋል፡፡
ሻምፒዮናውን በሴትም በወንደም ድምር ውጤት የኢትዮጵያ ንግድ 319 ዋንጨዋችን በመሰብሰብ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ፣ መቻል 315 ዋንጫዎችን…