ስፓርት
በዶሃ በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ የሩጫ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ በቀዳሚነት አጠናቀቀች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዶሃ በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ 1 ሺህ 500 ሜትር የሩጫ ውድድር ፍሬወይኒ ሀይሉ በቀዳሚነት አጠናቀቀች፡፡
አትሌቷ ውድድሩን 4:00.42 በሆነ ጊዜ በመግባት ነው ያሸነፈችው።
Read More...
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ።
ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሱሌማን ሀሚድ እና ፉዓድ ፈረጃ…
ኢትዮጵያ መድን ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ መድን ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ዛሬ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ የሊጉ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ብሩክ ሙሉጌታ ባስቆጠራት ግብ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
ፋሲል ከነማ እና ባህርዳር ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ እና ባህርዳር ከተማን ያገናኛኘው የወንድማማቾች ደርቢ ባዶ ለባዶ በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቀቀ፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው የ24ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ተመጣጣኝ የጨዋታ እንቅስቃሴን አስተናግዷል።
ክለቦቹ በሊጉ 10 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ 7 ጊዜ በአቻ ውጤት…
በሻምፒየንስ ሊጉ ከሪያል ማድሪድና ባየርሙኒክ ለፍጻሜ አላፊው ዛሬ ይለያል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ለፍፃሜ ለማለፍ በሚካሄደው የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ እና ባየርንሙኒክ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ጨዋታው ምሽት 4 ሠዓት ላይ በሪያል ማድሪድ ሜዳ ሳንትያጎ ቤርናቢዩ የሚከናወን ይሆናል፡፡
በመጀመሪያው ዙር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በባየርሙኒክ ሜዳ አሊያንዝ አሬና ስታዲየም 2…
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ለፍጻሜ ለማለፍ ዛሬ ተጠባቂ ጨዋታ ይደረጋል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ለፍፃሜ ለማለፍ በሚካሄደው የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ የፈረንሳዩ ፓሪስ ሴን ዠርሜ (ፒ ኤ ሲ ጂ) እና የጀርመኑ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ጨዋታው ምሽት 4 ሠዓት ላይ በፒ ኤስ ጂ ሜዳ ፓርክ ዴስ ፕሪንስ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን የመጀመሪያ…
ቅዱስ ጊዮርጊስ የዋናው ቡድን ዋና አሠልጣኝ አገደ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ የዋናው ቡድን ዋና አሠልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታን ከማሰልጠን ተግባራቸው በጊዜዊነት አግዷል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የዋናውን ቡድን እንቅስቃሴ ገምግሟል፡፡
በዚህም አሠልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ የዋናው ቡድን ዋና…