ስፓርት
የኢትዮጵያ ታምርት የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ታምርት የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡
በውድድሩ ከ10 ሺህ በላይ ግለሰቦች እንዲሁም ከ22 ክለቦች የተወጣጡ አትሌቶች ተሳትፈዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተመርተው ለዓለም አቀፍ ክለቦች የሚቀርቡ የስፖርት ትጥቆችን ማስተዋወቅ የሩጫው ዓላማ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
መርሐ ግብሩ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለማምረት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የውጭ ምንዛሬ ወጪን በማዳን ውጤት እያስገኘ መሆኑም ተመላክቷል፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር…
Read More...
ወላይታ ድቻ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 22ኛ ሳምንት ወላይታ ድቻ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ዛሬ 1:00 ላይ በተካሄደው ጨዋታ ለወላይታ ድቻ የማሸነፊያዋን ጎል ዘላለም አባተ በ80ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በተመሳሳት ቀን 10:00 ላይ በተካሄደው የሊጉ የድሬዳዋ ከተማና የሻሸመኔ…
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በነገው የለንደን ማራቶን ላይ ይወዳደራሉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለማችን ታዋቂ አትሌቶች የሚሳተፉበት የ2024 የለንደን ማራቶን በነገው ዕለት ይካሄዳል፡፡
በውድድሩ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉ ሲሆን÷ በወንዶች አትሌት ቀነኒሳ በቀለ፣ ሞስነት ገረመውና ታምራት ቶላ የአሸናፊነት ግምት ተሰጥቷቸዋል።
በሴቶች ደግሞ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው፣ ትዕግስት አሰፋና አልማዝ…
አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በ1 ሺህ 500 ሜትር በታሪክ ሶስተኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በ1 ሺህ 500 ሜትር ርቀት በታሪክ ሶስተኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸነፈች።
በቻይና ዝያሜን እየተካሄደ ባለው ዲያመንድ ሊግ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ 3:50.30 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀች ሲሆን፤ የገባችበት ሰዓት በርቀቱ በታሪክ ሶስተኛው ፈጣን ሰዓት መሆኑን የዓለም…
አትሌት ለሜቻ ግርማ በቻይና በተካሄደ 5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ለሜቻ ግርማ በቻይና ዢያሜን በተካሄደ የዲያመንድ ሊግ 5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈ።
12:58.96 በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀው አትሌት ለሜቻ ግርማ፤ በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል በርካታ ድል በማስመዝገብ የሚታወቅ አትሌት ነው።
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀዋሳ ከተማ አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው 22ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀዋሳ ከተማ ሀምበሪቾን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ቀን 10፡00 ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሀዋሳ ከተማን ለድል ያበቃውን ጎል የሀምበሪቾው ዲንክ ኪያር በራሱ ላይ አስቆጥሯል።
በተመሳሳይ ቀን 1:00 ላይ የተካሄደው የፋሲል ከነማ እና የአዳማ ከተማ…
በማንዴላ መታሰቢያ ዋንጫ ሚሊዮን ጨፎ የደቡብ አፍሪካ አቻዋን በበቃኝ አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ እየተካሄደ ባለው የማንዴላ መታሰቢያ ዋንጫ የቦክስ ውድድር ሚሊዮን ጨፎ የደቡብ አፍሪካ አቻዋን በበቃኝ አሸንፋለች፡፡
በ60 ኪሎግራም የደቡብ አፍሪካ አቻዋን የገጠመችው ቦክሰኛዋ በውድድሩ ሁለተኛ ዙር ላይ ተጋጣሚዋ ላይ ባሰረፈችው ቡጢ በዳኛ ውሳኔ አማካኝነት በበቃኝ ማሸነፍ ችላለች።…