ስፓርት
በፓሪስ ኦሊምፒክ ውድድሮች ኢትዮጵያን የሚወክሉ የመጨረሻ ተሰላፊ አትሌቶች ከነተጠባባቂያቸው ተለዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ውድድሮች በአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን የሚወክሉ የመጨረሻ ተሰላፊ አትሌቶች ከነተጠባባቂያቸው መለየታቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
በዚህም ፡-
800 ሜትር ሴቶች አትሌት ፅጌ ድጉማ፣አትሌት ሐብታም ዓለሙ፣አትሌት ወርቅነሽ መለሰ፣አትሌት ንግስት ጌታቸው (ተጠባባቂ)
1ሺህ 500 ሜትር በወንዶች አትሌት አብዲሳ ፈይሳ፣አትሌት ሳሙኤል ተፈራ፣አትሌት ኤርሚያስ ግርማ፣አትሌት ታደሰ ለሚ (ተጠባባቂ)
1ሺህ 500 ሜትር ሴቶች አትሌት ጉዳፍ…
Read More...
የቱርኩ የመሐል ተከላካይ ዴሚራል የሁለት ጨዋታ እገዳ ተጣለበት
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቱርኩ የመሐል ተከላካይ ሜሪህ ዴሚራል ሀገሩ ቱርክ ከኦስትሪያ ጋር በነበረው ጨዋታ ግብ ካስቆጠረ በኋላ ባሳየው አወዛጋቢ የደስታ አገላለፅ ምልክት በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ሁለት ጨዋታ እንዲታገድ ተደርጓል፡፡
የ26 ዓመቱ ዴሚራል በአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ኦስትሪያ ላይ ጎል ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን ለመግለፅ…
በአውሮፓ ዋንጫ ጀርመንና ስፔን የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር አዘጋጇ ጀርመን ከስፔን ጋር የምታደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡
የ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡
በዚህ መሰረትም አዘጋጇ ጀርመን እና ስፔን ምሽት 1 ሰዓት ላይ በስቱትጋርት አሬና ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ…
ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 4 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ዛሬ 9:00 ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ አማኑኤል ኤርቦ (ሁለት)፣ ዳዊት ተፈራ እና ተገኑ ተሾመ ባስቆጠሯቸው ግቦች አሸንፎ ወጥቷል።
በተመሳሳይ በፕሪሚየር ሊጉ ምሽት ላይ በተካሄደ…
ለ2025ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ ከዲሞክራቲክ ኮንጎ፣ ጊኒ እና ታንዛኒያ ጋር ተደለደለች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የ2025ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ኢትዮጵያ ከዲሞክራቲክ ኮንጎ፣ ጊኒ እና ታንዛኒያ ጋር ተደልድላለች።
የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌደሬሽን ካፍ የ2025ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ምድብ ድልድል ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሰረት ካሉት 12 ምድቦች ኢትዮጵያ በምድብ 8 ተደልድላለች።…
ሀድያ ሆሳዕና ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ30ኛ ሣምንት ጨዋታ መርሐ ግብር ሀድያ ሆሳዕና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 ረትቷል፡፡
ምንም እንኳ ኢትዮጵያ ቡና በአንተነህ ተፈራ ጎል ሲመራ ቢቆይም÷ የኋላእሸት ሰለሞን ለሀድያ ሆሳዕና ባስቆጠራቸው ሁለት ጎሎች ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
ቀደም ብሎ በተካሄደው የ30ኛ ሣምንት መርሐ-ግብር…
የ2017 የውድድር ዘመን የተጫዋቾች የዝውውር ጊዜ ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2017 የውድድር ዘመን የተጫዋቾች የዝውውር ጊዜ ይፋ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡
በዚህም መሠረት ከሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የዝውውር ጊዜው ክፍት ሆኖ ይቆያል መባሉን የፌደሬሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡