ስፓርት
የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ14ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ዛሬ የተካሄዱ ሁለት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቅቀዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት አዳማ ከተማ ከፋሲል ከነማ ያደረጉት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
የፋሲል ከነማን ብቸኛ ግብ ጌታነህ ከበደ ሲያስቆጥር÷ሲቦና ዓሊ ደግሞ ለአዳማ ከተማ አስቆጥሯል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሻሸመኔ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ ያደረጉት ጨዋታም በተመሳሳይ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
ግቦቹንም አለን ካይዋ ለሻሸመኔ ከተማ ሲያስቆጥር÷…
Read More...
አቶ ኢሳያስ ጅራ የካፍ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመረጡ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመርጠዋል፡፡
ካፍ ባደረገው ስብሰባ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አድርጎ መምረጡን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡…
በፕሪሚየር ሊጉ ባህርዳር ከነማ 4ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል
አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ14ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚርሊግ ባህርዳር ከተማ 4ኛ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕናን የገጠመው የአሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው ቡድን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ የነበረው ባህርዳር ከተማ የውጤት ቀውስ ውስጥ ገብቷል፡፡…
በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና እና ሲዳማ ቡና ድል ቀናቸው
አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው እለት በተካሄደው 14ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና እና ሲዳማ ቡና ድል ቀንቷቸዋል፡፡
9፡00 ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የሲዳማ ቡናን የማሸነፊያ ጎሎች በዛብህ መለዮ እና…
የጃፓኗ ካሳማ ከተማ ከንቲባ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስፖርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጃፓኗ ካሳማ ከተማ ከንቲባ ሺንጁ ያማጉቺ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተለያዩ የስፖርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል።
በጃፓን ካሳማ ከተማ ላለፋት ተከታታይ አምስት ዓመታት በታሕሳስ ወር በጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ በቂላ ለመዘከር የግማሽ ማራቶን ውድድር ይዘጋጃል ተብሏል፡፡
ከንቲባ ሺንጁ ያማጉቺ ዛሬ ለኢትዮጵያ…
የፊፋ ቴክኒካል ልዑክ ድሬዳዋ ገባ
አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ቴክኒካል ልዑክ ድሬዳዋ ከተማ ገብቷል፡፡
ልዑኩ ድሬዳዋ ከተማ የገባው የድሬዳዋ ስታዲየም የአርቴፊሻል ሳር ንጣፍ እድሳት መጠናቀቅን ተከትሎ ሙያዊ ምልከታ ለማድረግ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በምልከታውም ስታዲየሙ የፊፋን መስፈርት የሚያሟላ መሆኑን የማረጋገጥ ሥራ እንደሚያከናውን ይጠበቃል…
አሰልጣኝ ፍሬው ሀይለገብርኤል ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን እና ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር በይፋ ተለያይተዋል።
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆነው በ2013 ዓ.ም የተሾሙት አሰልጣኙ፤ በአራት ዓመት ቆይታቸው ቡድኑ በፈረንጆቹ 2022 እና 2024 የዓለም ዋንጫ…