Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በሊጉ የበዓል ሰሞን መርሐ-ግብር ማንቼስተር ሲቲ ከአስቶንቪላ፤ክሪስታል ፓላስ ከአርሰናል ዛሬ ይጫወታሉ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ማንቼስተር ሲቲ ከአስቶንቪላ እንዲሁም ክሪስታል ፓላስ ከአርሴናል ዛሬ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ። በከፍተኛ የውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ወደቪላ ፓርክ ተጉዞ ከቀኑ 9:30 ላይ ከአስቶን ቪላ ጋር በሚያከናውነው ጨዋታ ከባድ ፈተና እንደሚጠብቀው ይገመታል። በአውሮፓውያኑ የገና በዓል ሰሞን ጨዋታዎች ምሽት 12 ላይ ቀጥለው ሲካሔዱ÷ ብሬንትፎርድ አራተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ኖቲንግሃም ፎሬስትን በሜዳው ጂቴክ…
Read More...

አትሌት ድርቤ  በግራንድ ስላም ትራክ ውድድር ለመሳተፍ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አትሌት ድርቤ ወልተጂ የግል የውድድር መድረክ በሆነው የግራንድ ስላም ትራክ  ውድድር ላይ ለመሳተፍ የሚያስችል የኮንትራት ስምምነት ፈርማለች፡፡ በስምምነቱ መሰረት በ1 ሺህ 500 ሜትር  ርቀት ላይ በመወዳደር የምትታወቀው አትሌት ድርቤ በ2025 በአሜሪካ በሚደረገው የግራንድ ስላም ትራክ ውድድር ላይ ትሳተፋለች፡፡…

ለማህበራዊ ሚዲያ ጥቃት ለተጋለጡ 25 አትሌቶች የኤአይ ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለም አትሌቲክስ 25 የተለያዩ ሀገራት አትሌቶች ራሳቸውን ከማህበራዊ ሚዲያ ጥቃት እንዲከላከሉ የሚያስችል የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ (ኤአይ) ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ ተቋሙ ባደረገው የአራት ዓመታት ጥናት አትሌቶቹ ለከፋ የማህበራዊ ሚዲያ ጥቃት ተጋላጭ መሆናቸው ተገልጿል። በመሆኑም የማህበራዊ ሚዲያ ጥቃት…

ሪያል ማድሪድ የኢንተርኮንቲኔንታል ካፕ ዋንጫን አነሳ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ የ2024 የፊፋ ኢንተርኮንቲኔንታል ካፕ ዋንጫን አንስቷል፡፡ ማድሪድ ዋንጫውን ለማንሳት የበቃው ከሜክሲኮው ክለብ ፓቹካ ጋር ያደረገውን የፍፃሜ ጨዋታ 3 ለ 0 በመርታት ነው፡፡ ኪሊያን ምባፔ፣ ሮድሪጎ እና ቪኒሺየስ ጁኒየር ደግሞ ግቦቹን ከመረብ ማሳረፋቸውን ቢቢሲ ስፖርት ዘግቧል፡፡

ቪኒሺየስ ጁኒየር የፊፋ የአመቱ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)ብራዚላዊው የሪያል ማድረዱ ተጫዋች ቪኒሽየስ ጁኒየር የ2024 የፊፋ የወንዶች ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ። ተጫዋቹ በውድድር ዓመቱ ለሪያል ማድሪድ የስፔን ላሊጋንና የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ እንዲያሸንፍ ከፍተኛ አስተፅኦ አድርጓል። ተጫዋቹ ለቡድኑ 24 ጎሎችን አስቆጥሮ 11 ለግብ የሚሆኑ ኳሶች አመቻችቶ አቀብሏል።…

ሙድሪክ በጊዜያዊነት ከዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ውድድሮች ታገደ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዩክሬናዊው የቼልሲ የክንፍ መስመር ተጫዋች ሚካዬሎ ሙድሪክ በጊዜያዊነት ከዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ውድድሮች መታገዱ ተረጋግጧል፡፡ ውሳኔው የተላለፈው ተጫዋቹ ያልተፈቀደ አበረታች ቅመም ተጠቅሟል በሚል ምርመራ እየተደረገበት መሆኑን ተከትሎ ነው፡፡ ቼልሲ እና ተጫዋቹ ሙድሪክም የእንግሊዝ እግር ኳስ ማኅበር እያከናወነ…

ሮናልዶ ለፕሬዚዳንትነት እወዳደራለሁ አለ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የብራዚል እና ሪያል ማድሪድ የቀድሞ አንጋፋ ተጫዋች ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዲሊማ ለብራዚል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንትነት ልወዳደር ነው ብሏል፡፡ የ48 ዓመቱ የቀድሞ ዝነኛ ተጫዋች የወቅቱን የብራዚል እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኤድናልዶ ሮድሪጌዝ ለመተካት በሚደረገው ምርጫ በዕጩነት እንደሚቀርብ ይፋ አድርጓል፡፡…