Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስና ወላይታ ድቻ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ወላይታ ድቻ ሀምበሪቾ ዱራሜን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች አማኑኤል ኤርቦ፣ ፍሪምፖንግ ሜንሱ እና ሀብቶም ገብረእግዚያብሔር አስቆጥረዋል፡፡
Read More...

አቤል ያለው የግብጹን ዜድ ኤፍ ሲ ተቀላቀለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቅዱስ ጊዮርጊሱ አጥቂ አቤል ያለው የግብጹን ዜድ ኤፍ ሲ መቀላቀሉን ክለቡ አስታውቋል፡፡ ከታችኛው ሊግ በማደግ የግብጽ ፕሪሚየር ሊግን እየመራ የሚገኘው ዜድ ኤፍ ሲ  የቅዱስ ጊዮርጊሱን የፊት መስመር አጥቂ ለማስፈርም እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆቱ የሚታወስ ነው፡፡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ቀሪ የአንድ ዓመት ኮንትራት የነበረው…

ማሊ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ማሊ ቡርኪና ፋሶን 2ለ1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ማሊ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀል ችላለች፡፡ ሞሮኮ እና ደቡብ አፍሪካ ደግሞ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

የሀዋሳ ሃይቅ የግማሽ ማራቶን ውድድር የካቲት 3 ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 12ኛው የሀዋሳ ሃይቅ የግማሽ ማራቶን ውድድር የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚካሄድ ታላቁ ሩጫ አስታወቀ። ውድድሩ ከዚህ ቀደም ይታወቅበት የነበረውን ስያሜ በመቀየር "የሀዋሳ ሃይቅ ግማሽ ማራቶን" በሚል ይካሄዳል ነው የተባለው። በዘንድሮው ውድድር ከወትሮው በተለየ ከእንግሊዝ፣ ከአሜሪካ፣ ጆርጂያ፣…

ኬፕ ቨርዴ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ኬፕ ቨርዴ ሞሪታኒያን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡ ምሽት 2 ሰዓት በተደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ኬፕ ቨርዴ ሪያን ሜንዴዝ ባለቀ ደቂቃ ባስቆጠራት የፍጹም ቅጣት ምት 1 ለ 0 አሸንፋለቸ፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ኬፕ ቨርዴ በታሪኳ ለ2ኛ ጊዜ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀል ችላለች፡፡

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና ሲያሸንፍ ወላይታ ድቻና ሃድያ ሆሳዕና አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ወልቂጤ ከተማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የኢትዮጵያ ቡናን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አንተነህ ተፈራ በ33ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡ በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ…

የ2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ ሀገር አቀፍ የችቦ ቅብብሎሽ በመቀሌ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንጆቹ የ2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ ሀገር አቀፍ የችቦ ቅብብሎሽ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በመቀሌ ከተማ ተከሂዷል። በችቦ ቅብብሎሽ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብሩ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉ እና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል። መርሐ-ግብሩ በመጪው ሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ለሚካሄደው…