ስፓርት
አትሌት ለሜቻ ግርማ በፈረንሳይ ሌቪን በሚካሄደው የ3 ሺህ ሜትር ውድድር ይሳተፋል
አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ክብረ ወሰን ባለቤት ለሜቻ ግርማ በፈረንሳይ ሌቪን በሚካሄደው የ3 ሺህ ሜትር ውድድር እንደሚሳተፍ ተገለፀ፡፡
አትሌቱ ባለፈው የውድድር ዘመን በፈረንሳይ ሌቪን በ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር በ7 ደቂቃ 23 ሰከንድ 81 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሪከርድ ማሻሻሉ የሚታወስ ነው፡፡
ክብረወሰኑ ለ25 ዓመታት በኬንያዊው አትሌት ዳንኤል ኮመን ተይዞ መቆየቱም አይዘነጋም፡፡
የፈረንሳይ ሌቪን የቤት ወስጥ ውድድር የካቲት 10 የሚደረግ ሲሆን አትሌት ለሜቻ ከዚህ…
Read More...
የጊኒ ብሔራዊ ቡድን ማሸነፉን ተከትሎ ደስታቸውን በአደባባይ ሲገልፁ የነበሩ 6 ደጋፊዎች ህይወታቸው አለፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ጊኒ ጋምቢያን ማሸነፏን ተከትሎ ደስታቸውን በአደባባይ ሲገልፁ የነበሩ ስድስት ደጋፊዎች ህይዎታቸው ማለፉ ተገለፀ፡፡
ክስተቱን ተከትሎም የሀገሪቱ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የቀድሞው የጊኒ ኮከብ ተጫዋች ፓስካል ፊንዶኖ ደጋፊዎች እንዲረጋጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በአፍሪካ ዋንጫ 15 ጊዜ መሳተፍ የቻለችው ምዕራብ…
ሞሮኮ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ሞሮኮ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ አንድ አቻ ተለያይተዋል፡፡
11 ሰዓት ላይ በተካሄደው የምድብ 6 ጨዋታ ለሞሮኮ አሽራፍ ሀኪሚ እንዲሁም ለዲሞክራቲክ ኮንጎ ካቶምፓ ሙቩምፓ ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡
ዲሞክራቲክ ኮንጎ ያገኘቻትን የፍፁም ቅጣት ምት አጥቂው ሴድሪች ማካምቡ ሳይጠቀምበት…
ኢትዮጵያ ከኮሎምቢያ የዓለም ዋንጫ ውጭ ሆነች
አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር ጨዋታውን ከሞሮኮ አቻው ጋር አድርጓል፡፡
ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የተደረገውን የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ በፀሐይነሽ ጁላ ጎል ሞሮኮን 1 ለ 0 ብታሸንፍም÷ በድምር ውጤት 2 ለ 1 ተሸንፋ ከኮሎምቢያው የዓለም ዋንጫ ውጭ ሆናለች፡፡…
በታታ ሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው
አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2016 ( ኤፍ ቢ ሲ) በህንድ በተካሄደ የታታ ሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ስምንተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቁ፡፡
በሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ስምንተኛ ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቁ ሲሆን ÷አበራሽ ምንሰዎ ፣ሙሉሃብት ፅጌ እና መድህን በጀኔ ከአንደኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ…
በአፍሪካ ዋንጫ አንጎላ ሞሪታኒያን 3 ለ 2 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አንጎላ ሞሪታኒያን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡
ውጤቱን ተከትሎ አንጎላ ከቡርኪናፋሶ እኩል በአራት ነጥብ እና በአንድ ንጹሕ ግብ ምድቡን መምራት ችላለች፡፡
በአንጻሩ ሞሪታኒያ ያለምንም ነጥብ በምድብ አራት ግርጌ ላይ ተቀምጣለች፡፡
አርሰናል ክርስታል ፓላስን 5 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በተካሄደው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አርሰናል ክርስታል ፓላስን 5 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸነፈ፡፡
የአርሰናልን ጎሎች ገብርዔል ማጋሌስ በ11ኛው፣ ሄንደርሰን በራሱ ጎል ላይ በ37ኛው ደቂቃ፣ ትሮሳርድ በ59ኛው እንዲሁም ገብርኤል ማርቲኔሊ በ94ኛው እና በ95ኛው ደቂቃዎች ላይ አስቆጥረዋል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና…