Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

40ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ ማራቶን ውድድር ሰኔ 30 ይካሄዳል- ፌደሬሽኑ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰኔ 16 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 40ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ ማራቶን ውድድር ወደ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም መራዘሙን አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡ በተመሳሳይ ከሰኔ 11 እስከ 15 ቀን 2016 ሊካሄድ የነበረው 12ኛው ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሰኔ 25 እስከ 29 ቀን እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡ ውድድሮቹ የሚካሄዱት በሐዋሳ ከተማ መሆኑን የፌደሬሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡ ፌደሬሽኑ ለሁሉም ክልሎች፣ ከተማ አሥተዳደሮች፣ ክለቦች፣ ተቋማት እና የግል ተወዳዳሪዎች…
Read More...

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ቫር ሥራ ላይ መዋሉ እንዲቀጥል ወሰኑ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በቪዲዮ የተደገፈ ዳኝነት (ቫር) በሚቀጥለው የውድድር ዘመንም ሥራ ላይ መዋሉ እንዲቀጥል ወሰኑ፡፡ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 20 ክለቦች ቫር ሥራ ላይ መዋሉ ‘‘ይቀጥል ወይስ ይቋረጥ?’’ በሚል ሀሳብ ላይ ድምጽ ሰጥተዋል፡፡ በዚሁ መሰረት 19ኙ ክለቦች ቫር ሥራ ላይ መዋሉን እንዲቀጥል…

የፕሪሚየር ሊጉ ቀሪ ጨዋታዎች በሐዋሳ እንደሚካሄዱ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ27 እስከ 30ኛ ሣምንት ያሉ ጨዋታዎች በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም መካሄዳቸው እንደሚቀጥል ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ አክሲዮን ማኅበር እንዳስታወቀው÷ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ መልስ የፕሪሚየር ሊጉ የ27ኛ ሣምንት ጨዋታዎች ሐሙስ ሰኔ 6 ቀን 2016 ይጀምራሉ፡፡…

ኤንዞ ማሬስካ የቼልሲ አሰልጣኝ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ44 ዓመቱ ጣልያናዊው አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ ቼልሲን በዋና አሰልጣኝነት ለመምራት በይፋ ፊርማውን አስቀምጧል፡፡ ተሰናባቹን አሰልጣኝ ሞሪሲዮ ፖቼቲኖ ተክቶ እስከ ፈረንጆቹ 2029 የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ለማሰልጠን ለፈረመው ማሬስካ ዝውውር ቸልሲ 10 ሚሊየን ዩሮ እንደሚከፍል ተገልጿል፡፡ ከዝውውሩ ጋር የተያያዙ…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ቢሳው አቀና

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ ቢሳው ጋር ለሚያደርገው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ መዲናዋ ቢሳው ተጉዟል። 23 ተጫዋቾችን ያካተተው ልዑካን ቡድኑ ከአዲስ አበባ በቶጎ (ሎሜ) አድርጎ ቢሳው ከተማ ዛሬ ምሽት ላይ እንደሚደርስ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ ብሔራዊ ቡድኑ ለዓለም ዋንጫ…

በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ለሜቻ ግርማ የዓመቱን የዓለም ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስዊድን በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት አትሌት ለሜቻ ግርማ የዓመቱን የዓለም ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸነፈ፡፡ በዚህም መሠረት በ3 ሺህ ሜትር መሠናክል የወንዶች ውድድር አትሌት ለሜቻ ግርማ 8 ደቂቃ ከ1 ሰከንድ ከ63 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሲያሸንፍ÷ ሳሙኤል…

በማድሪድ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር ጥሩነሽ ዲባባ 3ኛ ስትወጣ ዳዊት ወልዴ በቀደሚነት አጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ማድሪድ በተካሄደው የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በሴቶች አንጋፋዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። በወንዶች ደግሞ ዳዊት ወልዴ በቀዳሚነት አጠናቋል፡፡ ጥሩነሽ 10 ኪሎ ሜትሩን በ30 ደቂቃ ከ03 ሴኮንድ በመጨረስ ነው 3ኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው፡፡ በወንዶች የ10 ኪሎ ሜትር…