Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን አገኘች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን አግኝታለች፡፡ ዛሬ በተደረገው ከ23 አመት በታች የነጠላ ወንዶች ብስክሌት ውድድር ኪያ ጀማል 2ኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አግኝቷል። ደቡብ አፍሪካ ውድድሩን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ ሞሪሺየስ 3ኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። በብስክሌት ኢትዮጵያ የመጨረሻ ውድድሯን በነገው እለት በድብልቅ ዘርፍ ታደርጋለች። በሰለሞን በቀለ
Read More...

የዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍፃሜ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023/24 የዩሮፓ ሊግ የሩብ ፍፃሜ ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ በድልድሉ መሠረትም ኤሲ ሚላን ከሮማ የሚፋለሙ ይሆናል፡፡ እንዲሁም ሊቨርፑል ከአታላንታ÷ ባየርሊቨርኩሰን ከዌስትሃም ዩናይትድ  ጋር ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡ በሌላ በኩል ቤኔፊካ ከማርሴ ጋር መደልደላቸውን የወጣው መርሐ-ግብር ያመላክታል፡፡

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍጻሜ ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ በዚሁ መሠረትም አርሰናል ከባየርን ሙኒክ ጋር የሚገናኙ ይሆናል፡፡ እንዲሁም አትሌቲኮ ማድሪድ ከቦርሲያ ዶርትመንድ፤ ሪያል ማድሪድ ደግሞ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ተድልድለዋል፡፡ በተጨማሪም ፓሪሴንት ዠርሜይን ከባርሴሎና ጋር በሩብ ፍፃሜው የሚገናኙ ይሆናል፡፡…

በግራንድ አፍሪካን ራን ለሚሳተፉ አትሌቶች የመኪና ሽልማት ተዘጋጀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ዋሽንገተን ዲሲ በሚካሄደው የግራንድ አፍሪካ ራን ለሚሳተፉ አትሌቶች የመኪና ሽልማት መዘጋጀቱ ተገለፀ፡፡ ግራንድ አፍሪካን ራን በየአመቱ ጥቅምት በገባ በሁለተኛዉ ቅዳሜ በዋሺንግተን ዲሲ ከተማ የሚደረግ የ5 ኪሎሜትር የሩጫ ዉድድር ነዉ። በዚህ ውድድር ለሚሳተፉ በአሜሪካ ግዙፉ የቶዮታ መኪና አከፋፋይ የሆነው…

በአራት በመቶ ነፃ ቀዘፋ የውሃ ዋና ውድድር ኢትዮጵያ 4ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ጨዋታዎች በሴቶቹ ዘርፍ በተደረገው የአራት በመቶ ነፃ ቀዘፋ የውሃ ዋና ውድድር ኢትዮጵያ 4ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። አትሌቶቹ ርቀቱን ለመጨረስ 5 ደቂቃ 18 ሴኮንድ ከ96 ማይክሮ ሴኮንድ ወስዶባቸዋል። ግብፅ በርቀቱ የሻምፒዮናውን ክብረ ወሰን በማሻሻል የወርቅ ሜዳሊያ ስታገኝ፤ አልጄሪያ እና ዚምባቡዌ የብር…

ራፋኤል ቤኒቴዝ ከሴልታ ቪጎ አሰልጣኝነታቸው ተሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ራፋኤል ቤኒቴዝ ከስፔኑ ሴልታ ቪጎ ቡድን አሰልጣኝነታቸው ተሰናብተዋል፡፡ የሊቨርፑልና የቼልሲ የቀድሞ አሰልጣኝ የነበሩት ቤኒቴዝ የላሊጋውን ቡድን በአሰልጣኝነት የተረከቡት ባለፈው ሰኔ ወር ነበር፡፡ ሴልታ ቪጎ በራፋኤል ቤኒቴዝ አሰልጣኝነት ወቅት ካደረጋቸው 28 የላሊጋ ጨዋታዎች ውስጥ ማሸነፍ የቻለው 5ቱን…

41 ሀገራትን አቆራርጦ አዲስ አበባ የገባው የሠላም ተጓዥ ብስክሌተኛ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሞሮኮ ራባት የተነሳው ኮትዲቯራዊ የሠላም ተጓዥ ብስክሌተኛ ካቮሬ ካሪን 41 ሀገራትን አቆራርጦ 42ኛ መዳረሻው በሆነችው ኢትዮጵያ ተገኝቷል፡፡ ከዚህ በፊት ኢትዮጵያን በስም ብቻ ያውቃት እንደነበር ያስታወሰው የሠላም ተጓዡ÷ በአዲስ አበባ በተመለከተው ሁሉ መደነቁን እና መደሰቱን ተናግሯል፡፡ ኢትዮጵያ የአፍሪካ መዲና…