ስፓርት
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ናኦሚ ግርማ የአሜሪካ የ2023 የምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሳን ዲያጎ ዌቭ የሴቶች ቡድን እየተጫወተች የምትገኘው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ናኦሚ ግርማ የአሜሪካ የ2023 የሴቶች ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸንፋለች፡፡
በዚህም የ23 አመቷ ናኦሚ በአሜሪካ ሴቶች እግርኳስ ታሪክ የመጀመሪያዋ ተከላካይ እና ሁለተኛዋ ጥቁር የአመቱ ምርጥ ሴት ተጫዋች ሽልማት አሸናፊ መሆን ችላለች፡፡
ናኦሚ የአሜሪካ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በ2023 ባደረጋቸው 16 የፊፋ የሴቶች የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ የቡድኑን የተከላካይ ክፍል በብቃት መምራቷ ተገልጿል፡፡
ከሽልማቱ…
Read More...
በፕሪሚየር ሊጉ ድሬደዋ ከተማ ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት የውድድር መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ ድሬደዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ያካሄዱት ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
የድሬደዋ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ቻርለስ ሙሰጌና ካርሎስ ዳምጠው ሲያስቀጥሩ÷የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ ግብ ደግሞ ወገኔ…
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጣለ
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው 10ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ ተለያይቷል፡፡
9፡00 ላይ ሐዋሳ ከተማን የገጠመው መቻል 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
የመቻልን ጎሎችም ምንይሉ ወንድሙ እና ከንዓን ማርክነህ ሲያስቆጥሩ÷ የሐዋሳ ከተማን ብቸኛ ጎል አሊ ሱለይማን…
ለአፍሪካ ዋንጫ የተለያዩ ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች አቢጃን እየገቡ ነው
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚደረገው የ2023ቱ የአፍሪካ ዋንጫ የተለያዩ ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች ወደ አቢጃን እየገቡ ይገኛሉ፡፡
ትናንት ምሽት የካሜሮኑ የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን ኮትዲቯር የገባ ሲሆን÷ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ከልዑካን ቡድኑ ጋር አቢጃን ገብተዋል፡፡
የካሜሮኑ የአፍሪካ…
የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት የውድድር መርሐ ግብር የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ ሻሸመኔ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ያካሄዱት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
የሻሸመኔ ከተማን ግብ አብዱልቃድር ናስር ሲያስቆጥር÷ኢትዮጵያ ቡናን አቻ ያደረገችዋን ግብ ደግሞ…
ፍራንዝ ቤከንባወር ከዚህ አለም በሞት ተለየ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የቀድሞው የምዕራብ ጀርመን እና የባየርሙኒክ ኮከብ ፍራንዝ ቤከንባወር በ78 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ቤከንባወር በ1974 ጀርመን የዓለም ዋንጫን ስታነሳ ብሄራዊ ቡድኑን በአምበልነት መምራት የቻለ ሲሆን ÷በ1990 ደግሞ የጀርመን ብሄራዊ ቡድንን በአሰልጣኝነት እየመራ የዓለም ዋንጫን ማንሳት ችሏል፡፡
ባለ…
በዱባይ እና ዥያሜን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2024 የዱባይ እና ዥያሜን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡
በዱባይ በወንዶች የተካሄደውን ውድድር አትሌት አዲሱ ጎበና ሲያሸንፍ÷ ለሚ ዱሜቻ 2ኛ፣ ደጀኔ መገርሳ 3ኛ እንዲሁም አብዲ ፉፋ 4ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡
በዚሁ የውድድር መርሐ-ግብር÷ አትሌት አንተን አየሁ ዳኛቸው 6ኛ፣…