ስፓርት
ኪሊያን ምባፔ ወደ ማድሪድ ተመለሰ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ26 ዓመቱ ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ወደ ሪያል ማድሪድ ተመልሷል፡፡
ትናንት ምሽት ፈረንሳይ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ዩክሬንን 4 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ቢያስቆጥርም ጉዳት አጋጥሞታል፡፡
በዚህም ተጫዋቹ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ስብስብን በመልቀቅ ወደ ክለቡ ሪያል ማድሪድ ለመመለስ ተገድዷል፡፡
ኪሊያን ምባፔ በቀኝ ቁርጭምጭሚቱ ላይ እብጠት እንዳጋጠመው የተገለፀ ሲሆን÷ ተጨማሪ የሕክምና ምርመራ በማድሪድ እንደሚደረግለት ነው የተጠቆመው፡፡
ፈረንሳዊው…
Read More...
ሚኬል አርቴታ አማትሪያን…
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል መሪ ሚኬል አርቴታ አማትሪያን የተወለደው በፈረንጆቹ 1982 በስፔን ሳን ሴባስቲያን ሲሆን፤ የእግር ኳስ ህይወቱ ጅማሬና ዕድገት በካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ነው፡፡
በባርሴሎና የታሰበውን ያክል የጨዋታ ጊዜ ባለማግኘቱ ወደ ፈረንሳዩ ክለብ ፓሪስ ሴን ዠርመ በማቅናት 18 ወራትን በውሰት አሳልፏል፡፡…
ሰር ዴቪድ ጆሴፍ ቤካም…
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ባህል እና እግር ኳስ ልዩ መለያ - ሰር ዴቪድ ጆሴፍ ቤካም፡፡
ትውልዱ በፈረንጆቹ 1975 በእንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን የሆነው ዴቪድ ቤካም የእንግሊዝ እግር ኳስ እና ባህል ልዩ መለያ ነው፡፡
የቀድሞ አማካይ በአራት የተለያዩ ሀገራት ሊጎች በመጫወት ዋንጫዎችን ያሸነፈ ብቸኛው እንግሊዛዊ ተጫዋች…
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ባህል ስፖርት ም/ፕሬዚዳንት ቦታን ማግኘቷ የሚበረታታ ነው – ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 1 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ባህል ስፖርት አባል ሀገር ከመሆን አልፋ የምክትል ፕሬዚዳንትነት ቦታን ማግኘቷ የሚበረታታ ነው አሉ የኢትዮጵያ ባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ።
የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ…
አስቶንቪላ ድል ሲቀናው ኒውካስል ዩናይትድ ተሸንፏል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወደ ቴክ ኮሚኒቲ ስቴዲየም በማቅናት ብሬንትፎርድን የገጠመው ኒውካስል ዩናይትድ 3 ለ 1 ሲሸነፍ አስቶንቪላ በአንጻሩ ቦርንማውዝን 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡
11 ሰዓት ላይ በተከናወነው ጨዋታ የብሬንትፎርድን የማሸነፊያ ግቦች ሻዴ እና ኢጎር ቲያጎ (2) ሲያስቆጥሩ የኒውካስልን ብቸኛ ግብ…
ሀዋሳ ከተማና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሀዋሳ ከተማን ግብ ያሬድ ብሩክ አስቆጥሯል፡፡
አዲስ ግደይ ደግሞ የንግድ ባንክን የአቻነት ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡…
ኢትዮጵያ ቡና በአዳማ ከተማ ተሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የአዳማ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ነቢል ኑሪ ከመረብ አሳርፏል፡፡
የኢትዮጵያ ቡናው በፍቃዱ ዓለማየሁ 73ኛው ደቂቃ ላይ በቀይ ካርድ ከሜዳ…