ስፓርት
ዌስትሃም ዩናይትድ አሰልጣኝ ግራሃም ፖተርን አሰናበተ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የለንደኑ ክለብ ዌስትሃም ዩናይትድ አሰልጣኝ ግራሃም ፖተርን ከኃላፊነታቸው አሰናብቷል፡፡
አሰልጣኙ ባለፈው የውድድር ዓመት አጋማሽ ክለቡን ከተረከቡ ወዲህ በቆይታቸው ካደረጉት 25 ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻሉት ስድስቱን ብቻ ነው፡፡
ዌስትሃም በፖተር ምትክ በቅርቡ ከኖቲንግሃም ፎረስት የተሰናበቱትን ኑኖ ስፕሪቶ ሳንቶን አሰልጣኙ ለማድረግ በንግግር ላይ መሆኑ ተነግሯል፡፡
ዌስትሃም ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊጉ በሦስት ነጥብ 19 ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ ከወዲሁ ከካራባኦ…
Read More...
ኢትዮጵያዊቷ ፅጌ ካሕሳይ በዓለም የብስክሌት ሻምፒዮና ከአፍሪካ በቀዳሚነት አጠናቀቀች
አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያዊቷ ፅጌ ካሕሳይ በዓለም የብስክሌት ሻምፒዮና በወጣቶች ዘርፍ ከአፍሪካ አንደኛ በመሆን አጠናቀቀች።
የዓለም የብስክሌት ሻምፒዮና በሩዋንዳ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህም ኢትዮጵያዊቷ ብስክሌተኛ ፅጌ ካሕሳይ 74 ኪሎ ሜትር በሸፈነው የወጣቶች የጎዳና ውድድር ከአፍሪካ አንደኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።…
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለተመዘገበው ደካማ ውጤት ይቅርታ ጠየቀ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለተመዘገበው ደካማ ውጤት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ይቅርታ ጠየቀ፡፡
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን 20ኛውን የቶኪዮ ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ቆይታ አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፤ አትሌቶች ለውድድሩ ጥሩ ዝግጅት ቢያደርጉም የተመዘገበው ውጤት የሚያስከፋ…
በሊጉ የመጀመሪያ ሣምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ይጫወታሉ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዕጣ ማውጣት ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ ቡናን ከቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያገናኘው ተጠባቂ ጨዋታ በመጀመሪያ ሣምንት የሚደረግ ይሆናል፡፡
በሌላ በኩል የአምና የሊጉ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን በመጀመሪያ ሣምንት ከአዳማ ከተማ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡…
በአዲሱ የውድድር ዘመን የሪያል ማድሪድ ጅማሮ …
አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ በ2024/25 የውድድር ዘመን ባለፉት ዓመታት ሲያደርግ እንደነበረው በዋንጫዎች የታጀበ ጊዜ ማሳለፍ አልቻለም ነበር።
በውድድር ዘመኑ በምንጊዜም ተቀናቃኙ ባርሴሎና ላሊጋውን ጨምሮ ሌሎች የውስጥ ውድድር ዋንጫዎችን ተነጥቋል።
ሪያል ማድሪድ የ2024/25 የውድድር ዓመት ከመጀመሩ አስቀድሞ ካለው የስብስብ…
ጋቪ በጉዳት ሳቢያ ለአምስት ወራት ከሜዳ ይርቃል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው የባርሴሎና ኮከብ ጋቪ በጉዳት ምክንያት ለአምስት ወራት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ተመላክቷል፡፡
የ21 ዓመቱ አማካይ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር በልምምድ ወቅት በደረሰበት የጉልበት ጉዳት ሳቢያ ነው ከሜዳ የሚርቀው፡፡
ተጫዋቹ በቀኝ እግሩ ጉልበት ላይ የደረሰበትን ጉዳት ተከትሎ ቀዶ ሕክምና…
የኢትዮጵያ አዳጊዎች ኦሊምፒክ በጥቅምት ወር ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሁለተኛው የኢትዮጵያ አዳጊዎች ኦሊምፒክ ጨዋታ በመጪው ጥቅምት ወር በአዲስ አበባ ይደረጋል አለ፡፡
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በሰጡት መግለጫ÷ በውድድሩ እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ አዳጊዎች ይሳተፋሉ፡፡
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ በአዳጊ…