ስፓርት
ማንቼስተር ዩናይትድ ቼልሲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአምስተኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በሜዳው ኦልድ ትራፎርድ ቼልሲን ያስተናገደው ማንቼስተር ዩናይትድ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ቡሩኖ ፈርናንዴዝ እና ካዚሜሮ ለማንቼሰተር ዩናይትድ ሲያስቆጥሩ የቼልሲን ብቸኛ ግብ ትሪቮ ቻሎባህ አስቆጥሯል፡፡
በጨዋታው የቼልሲው ግብ ጠባቂ ሮበርት ሳንቼዝ ገና በ4ኛው ደቂቃ እንዲሁም የማንቼስተር ዩናይትዱ አማካይ ካዚሜሮ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ወጥተዋል፡፡
Read More...
በመርሲሳይድ ደርቢ ሊቨርፑል ኤቨርተንን 2 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ሊቨርፑል ኤቨርተንን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
በአንፊልድ በተደረገው ጨዋታ ሪያን ግራቨንበርች እና ሁጉ ኢኪቲኬ የሊቨርፑልን ጎሎች ሲያስቆጥሩ የኤቨርተንን ብቸኛ ጎል ኤዲሪሳ ጉየ አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ሊቨርፑል ነጥቡን ወደ 15 ከፍ በማድረግ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡
ኢትዮጵያ በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ኬኒያ የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ አገኘች
አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጃፓን ቶኪዮ እየተካሄደ በሚገኘው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ኬኒያ የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ አገኘች አግኝታለች።
ኢትዮጵያ በውድድሩ በአትሌት ጉዳፍ ፀጋይ፣ መዲና ኢሳ እና ፋንታዬ በላይነህ ብትወከልም ድል ሳይቀናት ቀርቷል።
አትሌት ጉዳፍ 5ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን…
ማንቼስተር ዩናይትድ ከቼልሲ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ ከቼልሲ እንዲሁም በመርሲሳይድ ደርቢ ሊቨርፑል ከኤቨርተን የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ ከቼልሲ የሚያደርጉት ጨዋታ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ኦልድትራፎርድ ይካሄዳል።
የውድድር ዓመቱን በጥሩ ውጤት ያልጀመረው ማንቼስተር ዩናይተድ…
ወላይታ ድቻ እና አል ኢትሃድ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በካፍ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታ ወላይታ ድቻ ከአል ኢትሃድ ጋር ያለ ግብ አቻ ተለያይቷል።
በውድድሩ ኢትዮጵያን የሚወክለው ወላይታ ድቻ ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከሊቢያው አል ኢትሃድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቋል።
በአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራ የሚመሩት ወላይታ ድቻዎች የመልሱን…
ጆዜ ሞሪኒሆ የቤኔፊካ አሰልጣኝ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ የፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ አሰልጣኝ መሆናቸው ይፋ ሆነ።
ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ በቤኔፊካ እስከ ፈረንጆቹ 2027 የሚያቆያቸውን የሁለት ዓመት ኮንትራት ተፈራርመዋል።
ሞሪኒሆ ከዚህ ቀደም ሪያል ማድሪድ፣ ኢንተር ሚላን፣ ቼልሲ፣ ቶተንሃም ሆትስፐር እንዲሁም ፖርቶን የመሳሰሉ ክለቦችን ማሰልጠናቸው…
ኢትዮጵያ በሴቶች የ3ሺህ ሜትር መሰናክል የነሐስ ሜዳልያ አገኘች
አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በሴቶች የ3ሺህ ሜትር መሰናክል በሲምቦ አለማየሁ አማካኝነት ተጨማሪ የነሐስ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡
በርቀቱ ከአትሌት ሲምቦ አለማየሁ በተጨማሪ ኢትዮጵያን የወከለችው ሎሚ ሙለታ 8ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን አጠናቅቃለች፡፡
ውድድሩን ኬንያዊቷ አትሌት ፌይዝ ቼሮቲች በበላይነት…