ስፓርት
ወላይታ ድቻ እና መቐለ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ድቻ እና መቐለ 70 እንደርታ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታን ግቦች ቦና ዓሊ (በፍፁም ቅጣት ምት) እና ኪቲካ ጅማ አስቆጥረዋል፡፡
የወላይታ ድቻን የአቻነት ግቦች ደግሞ ምንተስኖት ተስፋዬ እና ካርሎስ ዳምጠው (በፍፁም ቅጣት ምት) ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ወላይታ ድቻ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያውን ነጥብ…
Read More...
በውድድር ዓመቱ 16ቱንም ጨዋታዎች ያሸነፈው ባየርን ሙኒክ…
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጀርመኑ ክለብ ባየርን ሙኒክ በዚህ የውድድር ዓመት በሁሉም ውድድር ያደረጋቸውን ሁሉንም ጨዋታዎች በማሸነፍ ስኬታማ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡
ባየርን ሙኒክ በውድድር ዓመቱ በሁሉም ውድድሮች ያደረጋቸውን 16 ተከታታይ ጨዋታዎች ድል በማድረግ ያለመሸነፍ ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
በአሰልጣኝ ቪንሰንት ኮምፓኒ የሚመራው…
የፊፋ የዓመቱ ምርጥ እጩዎች ይፋ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፊፋ የ2025 የዓመቱ ምርጥ እጩዎች በተለያዩ ዘርፎች ይፋ ተደርገዋል።
በአሰልጣኞች ዘርፍ ሉዊስ ኤኒሪኬ፣ አርኔ ስሎት፣ ሚካኤል አርቴታ፣ ኢንዞ ማሬስካ፣ ሀንሲ ፍሊክ እና ሮቤርቶ ማርቲኔዝ በዕጩነት ቀርበዋል።
በተጫዋቾች ዘርፍ ደግሞ የባሎንዶር አሸናፊው ኦስማን ዴምቤሌ፣ አሽራፍ ሀኪሚ፣ ሀሪ ኬን፣…
ፌዴሬሽኑ የአፍሪካ ባህል ስፖርቶች ኮንፌዴሬሽን አባልነት ማረጋገጫ ተሰጠው
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን አባል የሆነበትን የአፍሪካ ባህል ስፖርቶች ኮንፌዴሬሽን የአባልነት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት በዛሬው ዕለት ተሰጠው።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ህይወት መሃመድ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ÷ ጥያቄው አስቀድሞ ተቀባይነት ማግኘቱን ጠቅሰው÷ በዚምባብዌ ሃራሬ ከተማ በተካሄደው ዓመታዊ ጠቅላላ…
ዝምተኛው የእግር ኳስ ጥበበኛ ቶኒ ክሩስ…
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አቻ በሌለው እይታው እና መስመር ሰንጣቂ ኳሶቹ ይታወቃል ጀርመናዊ የእግር ኳስ ጥበበኛ ቶኒ ክሩስ፡፡
በፈረንጆቹ 1990 በምስራቅ ጀርመን ግሪፍስዋልድ የተወለደው ቶኒ ክሩስ÷ የእግር ኳስ ሕይወቱን ጅማሮ ያደረገው በአካባቢው በሚገኝ ግሪፍስዋልደር በተሰኘ ክለብ ነው፡፡
በ2007 በ17 ዓመቱ ለባየርን ሙኒክ ዋናው ቡድን…
ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች የጨረሰ ብቸኛው አትሌት… ኤሊዩድ ኪፕቾጌ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ገና በለጋ እድሜው ከቤት ወደ ትምህርት ቤት ደግሞም ከትምህርት መልስ ወደ ቤት ሦስት ኪሎ ሜትሮችን እለት እለት እየሮጠ ነው ያደገው፡፡
ትምህርትን አብዝቶ ይወድ ነበርና በጊዜው በትምህርት ፍቅሩ የተነሳ የሰርክ ተግባሩ የነበረው ሩጫ የማታ ማታ የስኬት ማማ መወጣጫ ሆኖታል።
በልጅነቱ አባቱን በሞት ማጣቱን ተከትሎ…
መቻል ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአራተኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መቻል ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የመቻልን ግቦች መሐመድ አበራ እና ብሩክ ማርቆስ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥረዋል፡፡
መቻል በውድድር ዓመቱ ሶስተኛ ድሉን ሲያሳካ፥ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እስካሁን አንድም ጨዋታ ማሸነፍ አልቻለም፡፡