ስፓርት
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያተይተዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ቴዎድሮስ ሀይለማሪያም ለወላይታ ድቻ እንዲሁም አቤል ያለው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡
ቀን 7 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ እና ፋሲል ከነማ በአዲስ አበባ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ ያለ ምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል።
የሊጉ ጨዋታ ቀጥሎ እየተካሄደ…
Read More...
በአፍሪካ ዋንጫ ሁለት የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሁለት የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ይደረጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ላይ ሴኔጋል ከሱዳን ጋር ይገናኛሉ።
በምድብ ጨዋታዎች ሴኔጋል ሁለቱን በማሸነፍ እና በአንድ ጨዋታ አቻ በመለያየት በሰባት ነጥብ ከምድቧ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለች ሲሆን፤ ሱዳን…
ማንቼስተር ሲቲ ከቼልሲ …
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ20ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ይጀምራሉ፡፡
አስቶንቪላ ከኖቲንግሃም ፎረስት በቪላ ፓርክ ቀን 9:30 ላይ የሚያርጉት ጨዋታ ቀዳሚው መርሐ ግብር ነው፡፡
ከ11 ተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ በሳምንቱ አጋማሽ በአርሰናል የተሸነፈው አስቶንቪላ ወደ ድል ለመመለስ ይፋለማል፡፡
ያለፉትን ሦስት…
አወዛጋቢው ኮከብ ማሪዮ ባላቶሊ…
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በነውጠኛ ባህሪው እና በአወዛጋቢ ድርጊቶቹ የሚታወቅ ተጫዋች ነው ማሪዮ ባላቶሊ፡፡
ማሪዮ ባላቶሊ ፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ሕይወቱን የጀመረው በሀገሩ ክለብ ሉሜዛን ሲሆን÷ ከዚያ በመቀጠል ለኢንተር ሚላን፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ ኤሲሚላን እና ሊቨርፑልን ለመሳሳሉ ታላላቅ ክለቦች መጫወቱ ይታወሳል፡፡
ከጣሊያኑ ክለብ ኢንተርሚላን…
ቼልሲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን አሰናበተ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን አሰናብቷል፡፡
የክለቡ ቦርድ በአሰልጣኙ ቆይታ ዙሪያ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የጣሊያናዊው አሰልጣኝ ውል እንዲቋረጥ ወስኗል፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2029 በክለቡ የሚያቆይ ውል የነበራቸው ኢንዞ ማሬስካ በስምምነት ከክለቡ ጋር መለያየታቸውን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ19ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ 2ኛ ላይ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ ይፋለማል፡፡…
አልጄሪያ እና ቡርኪና ፋሶ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ አልጄሪያ እና ቡርኪና ፋሶ አሸንፈዋል።
በምድብ አምስት ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ በአልጀሪያ ኢኳቶሪያል ጊኒን 3 ለ 1 አሸንፋለች።
የአልጀኢሪያን የማሸነፊያ ግቦች ኢብራሂም ማዛ፣ ፋሬስ ቻይቢ እና ዚነዲን ቤላይድ…