Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ቡካዮ ሳካ ከረዥም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ልምምድ ተመለሰ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርሰናሉ ወሳኝ ተጫዋች ቡካዮ ሳካ ከሶስት ወራት ጉዳት በኋላ ወደ ልምምድ መመለሱ ተነግሯል፡፡ ተጫዋቹ ከቡድኑ ጋር ልምምድ መስራቱ የተገለጸ ሲሆን፥ አርሰናል በቻምፒየንስ ሊጉ ከሪያል ማድሪድ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡ ቡካዮ ሳካ በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሁሉም ውድድሮች በጎል ተሳትፎ የክለቡ ቀዳሚ ተጫዋች ነው፡፡
Read More...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ የደጋፊዎች ድምጽ አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሰሞኑን በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በ1 ሺህ 500 ሜትር ርቅት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቷ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ የደጋፊዎች ድምጽ አሸናፊ ሆናለች፡፡ የዓለም አትሌቲክስ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ ባጋራው መረጃ፤ ከደጋፊዎች ባሰባሰበው ድምጽ መሠረት አትሌት ጉዳፍ ማሸነፏን አስታውቋል፡፡ በዓለም የቤት ውስጥ…

አርጀንቲና አራት ጨዋታ እየቀራት ወደ ዓለም ዋንጫ አለፈች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ አሜሪካ ሀገራት የ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከብራዚል ጋር ጨዋታዋን ያደረገችው አርጀንቲና 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች። የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ግቦች ዩሊያን አልቫሬዝ፣ ኢንዞ ፈርናንዴዝ፣ አሌክሲስ ማክ አሊስተር እና ጁሊያኖ ሲሞን ሲያስቆጥሩ፤ ብራዚልን ከሽንፈት ያልታደገች ብቸኛዋን ግብ ማቲያስ ኩንሀ…

ሴፕ ብላተር እና ሚሼል ፕላቲኒ ከቀረበባቸው ክስ በድጋሚ በነፃ ተሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ የፊፋ ፕሬዚዳንት ሴፕ ብላተር እና የቀድሞ የዩኤፋ ፕሬዚዳንት ሚሼል ፕላቲኒ ከቀረበባቸው በፊፋ የፋይናንሺያል የስነ ምግባር ጥሰት ክስ በነፃ መሰናበታቸው ተገልጿል። ሁለቱ የቀድሞ የእግር ኳስ ከፍተኛ ኃላፊዎች በፈረንጆቹ 2011 ላይ ፈፅመዋል ከተባሉበት የ2 ሚሊየን ዶላር ማጭበርበር ወንጀል ክስ በስዊዘርላንድ ፍርድ…

ሸገር ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አደገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ አንድ እየተሳተፈ የሚገኘው ሸገር ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል። ዛሬ የምድብ 18ኛ ጨዋታውን ያደረገው ሸገር ከተማ እንጅባራ ከተማን 5 ለ 1 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎ ነጥቡን 45 ያደረሰው ሸገር ከተማ አራት ጨዋታ እየቀረው አስቀድሞ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር…

ፔፕ ጋርዲዮላ በማንቼስተር ሲቲ…

ማንቼስተር ዩናይትድን በታሪክ ማማ ላይ የሰቀሉት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ፔፕ ጋርዲዮላ በፈረንጆቹ 2016 ወደ ማንቼስተር ሲቲ ሲመጣ ስለ ስፔናዊው አሰልጣኝ ተጠይቀው የሰጡት መልስ "ይህ ቡንደስ ሊጋ ወይም ስፔን ላሊጋ ሳይሆን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነው" የሚል ነበር፡፡ ይህ ምላሻቸውም ፔፕ በሁለቱ ሊጎች ያገኘውን ድል በፕሪሚየር ሊጉ መድገም አይችልም ለማለት እንደነበረ ግልጽ…

በቻይና ናንጂንግ የተሳተፈው ኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቻይና ናንጂንግ በተካሄደው 20ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቷል። የልዑካን ቡድኑ አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የጀግና አቀባበል የተደረገላቸው መሆኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ መረጃ አመላክቷል። ለልዑካኑ…