ስፓርት
ሀድያ ሆሳዕና እና ምድረ ገነት ሽረ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀድያ ሆሳዕና እና ምድረ ገነት ሽረ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የሀድያ ሆሳዕናን ግብ እዮብ አለማየሁ ሲያስቆጥር ዳንኤል ዳርጌ ደግሞ የምድረ ገነት ሽረን ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሸገር ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት…
Read More...
ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ መሆኑን ፎርብስ ይፋ አድርጓል፡፡
ፎርብስ መጽሔት በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት÷ ሪያል ማድሪድ በ9 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ዋጋ የዓለማችን ውዱ ክለብ መሆን ችሏል፡፡
ሪያል ማድሪድ በውድድር ዓመቱ ስኬታማ ጊዜ ባያሳልፍም ለተከታታይ አምስተኛ ዓመት…
ሚኬል አርቴታ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ሽልማትን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 ውድድር ዓመት ምርጥ አሰልጣኝ ሽልማትን አሸንፏል፡፡
ሚኬል አርቴታ በውድድር ዓመቱ የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ከአርሰናል ጋር ያነሳ ሲሆን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግም ክለቡን ለፍፃሜ አድርሷል።
አርሴን ቬንገር በፈረንጆቹ 2003/4 የፕሪሚየር ሊጉ…
ኤሲሚላን ከአሰልጣኝ ማሲሚሊያኖ አሌግሪ ጋር ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጣሊያኑ ክለብ ኤሲሚላን ከአሰልጣኝ ማሲሚሊያኖ አሌግሪ ጋር ተለያይቷል፡፡
ሚላን በሴሪ ኤው የውድድር ዓመቱ የመጨረሻ ጨዋታ በካግሊያሪ 2 ለ 1 መሸነፉን ተከትሎ 5ኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ ተገዷል፡፡
በዚህም በተከታታይ ሁለት ዓመታት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ቦታን ማግኘት ሳይችል ቀርቷል፡፡…
ሻምፒዮኑ አርሰናል ዋንጫውን ተረከበ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል በዛሬው ዕለት ዋንጫውን ተረክቧል፡፡
ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል÷ በዚህ ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ…
በኬፕ ታውን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳንላም ኬፕ ታውን የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡
በወንዶች አትሌት መሀመድ ኢሳ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ55 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል፡፡
በርቀቱ የተሳተፈው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ይሁንልኝ አዳነ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ በመግባት ሁለተኛ…
በሺያመን ዳይመንድ ሊግ አትሌት አዲሱ ይሁኔ አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዳይመንድ ሊግ ሁለተኛ መዳረሻ በሆነችው የቻይናዋ ሺያመን ከተማ በወንዶች 5 ሺህ ሜትር አዲሱ ይሁኔ አሸንፏል።
አትሌት አዲሱ 12፡57.32 በሆነ ሰዓት ውድድሩን ያጠናቀቀ ሲሆን ይህም የዓመቱ የዓለማችን ፈጣኑ ሰዓት እንዲሁም የውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።
ሌላኛው ኢትዮጵያዊው አትሌት ቢኒያም…