Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

4 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የዓመቱ ምርጥ አትሌት ዕጩ ውስጥ ተካተቱ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ታምራት ቶላ፣ ትዕግስት ከተማ እና ሱቱሜ አሰፋ የ2024 ከስታዲየም ውጭ የወንዶች የዓመቱ ምርጥ አትሌት ምርጫ ላይ በዕጩነት ተካተቱ፡፡ አትሌቶቹ በውድድር ዓመቱ በተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮች ባስመዘገቡት ውጤት ነው ለዕጩነት መካተት የቻሉት። በውድድር ዓመቱ አትሌት ታምራት ቶላ የኦሊምፒክ እና የበርሊን ማራቶንን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ እንዲሁም አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቫሌንሺያ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር የዓለም…
Read More...

አርሰናል እና ሊቨርፑል አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 9ኛ ሣምንት ጨዋታ በሜዳው ሊቨርፑልን ያስተናገደው አርሰናል 2 አቻ ተለያይቷል። 1 ሠዓት ከ30 ላይ በተካሄደው ጨዋታ፥ ቡካዮ ሳካ እና ሚኬል ሜሪኖ የመድፈኞቹን ግቦች አስቆጥረዋል። ቨርጅል ቫን ዳይክ እና ሞሐመድ ሳላህ ደግሞ የሊቨርፑልን ጎሎች ከመረብ አሳርፈዋል።…

ቼልሲ ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቼልሲ፣ ክሪስታል ፓላስ እና ዌስትሃም ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ ቼልሲ ከኒውካስል ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ግቦቹን ጃክሰን እና ፓልመር አስቆጥረዋል፡፡ የኒውካስልን ብቸኛ ግብ ደግሞ ኢሳቅ አስቆጥሯል፡፡ ክሪስታልፓላስ ቶተንሃምን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ግቧን ማቴታ አስቆጥሯል፡፡…

በፍራንክፈርት ማራቶን አትሌት ሀዊ ፈይሳ ክብረወሰን በማሻሻል አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀርመን ፍራንክፈርት በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ውድድር  አትሌት ሀዊ ፈይሳ ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፋለች። አትሌት ሀዊ ፈይሳ ውድድሩን  2 ሰዓት ከ17 ደቂቃ ከ25 ሰከንድ በመግባት ማሸነፏን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ የዓለም የግማሽ ማራቶን ክብረ ወሰንን ሰበረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቫሌንሺያ ሜዲዮ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረወሰንን በመስበር ጭምር አሸነፈ፡፡ አትሌቱ ርቀቱን ያጠናቀቀው 57 ደቂቃ ከ30 ሰከንድ በመግባት መሆኑን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ አመላክቷል፡፡ የዓለም የግማሽ ማራቶን ክብረወሰን በዑጋንዳዊው አትሌት  ጃኮብ ኪፕሊሞ ተይዞ መቆየቱ…

የኮምቦልቻ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎች የሰላም የእግር ጉዞ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮምቦልቻ ከተማ የሚገኙ የብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎች የሰላም የእግር የእግር ጉዞ አድርገዋል፡፡ የኮምቦልቻ ከተማ ከንቲባ ሙሐመድ አሚን በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር÷ ከተማዋ በሰላምና በልማት ጎዳና ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል፡፡ ከልማት የሚገኘውን ጥቅም ዘላቂ ለማድረግም ማኅበረሰቡ ሰላሙን አስጠብቆ መቀጠል እንዳለበት…

አርሰናል ከሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በ9ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዛሬው የጨዋታ መርሐ-ግብር መሠረት÷ ክሪስታል ፓላስ ከቶተንሃም ሆትስፐር፣ ቼልስ ከኒውካስል እንዲሁም ዌስትሃም ከማንቼስተር ዩናይትድ በተመሳሳይ 11 ሠዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡ በሌላ በኩል ምሽት 1 ሠዓት ከ30 ላይ አርሰናል ከሊቨርፑል የሚያደርጉት…