Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛ ሳንምት አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈ። በድሬዳዋ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ አዳማ ከተማ ስንታየሁ መንግስቱ ባስቆጠራቸው  ሁለት ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል። ኢትዮጵያ ቡና ከሽንፈት ያላዳነውን ብቸኛ ግብ አንተነህ ተፈራ አስቆጥሯል።
Read More...

የሲቲው አማካይ ሮድሪ ከተገመተው ጊዜ ቀድሞ ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የማንቼስተር ሲቲው የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ሮድሪ ከተገመተው ጊዜ ቀደም ብሎ ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል ተናግሯል፡፡ ተጫዋቹ ባለፈው መስከረም ወር ሲቲና አርሴናል 2 አቻ በተለያዩበት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በቀኝ ጉልበቱ ላይ ባጋጠመው ጉዳት የውድድር ዓመቱ እስከሚጠናቀቅ ከሜዳ እንደሚርቅ ሲነገር ቆይቷል፡፡…

ሩድ ቫን ኒስትሮይ የሌስተር ሲቲ አሰልጣኝ ለመሆን ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከማንቼስተር ዩናይትድ ምክትል አሰልጣኝነቱ በቅርቡ የለቀቀው ሩድ ቫን ኒስትሮይ የሌስተር ሲቲ አሰልጣኝ ለመሆን መስማማቱ ተገለፀ፡፡ ሆላንዳዊው አሰልጣኝ በውድድር ዓመቱ በሌስተር ሲቲ ቤት ደካማ አቋም ያሳዩትን ስቴቭ ኩፐርን በመተካት ነው በዋና አሰልጣኝነት ለመምራት የተስማማው፡፡ በስምምነቱ መሰረትም ቫን ኒስትሮይ ሌስተር…

ወርቅውሃ ጌታቸው በመላ አፍሪካ ጦር ሃይሎች ስፖርት ፌስቲቫል 2ኛ ወርቅ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ)በናይጄሪያ አቡጃ እየተካሄደ በሚገኘው 2ኛው የመላ አፍሪካ ጦር ሃይሎች ስፖርት ፌስቲቫል በ3 ሺህ ሜትር መሠናክል ሃምሳ አለቃ ወርቅውሃ ጌታቸው የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች። በዚህም አትሌቷ ለመከላከያው መቻል ስድስተኛ፤ ለራሷ ደግሞ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ማስመዝገብ ችላለች። ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የ3 ሺህ መሠናክል…

ላሚን ያማል የ2024 ወርቃማ ታዳጊ ተጫዋች ሽልማትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የባርሴሎና እና የስፔን ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ላሚን ያማል የ2024 ወርቃማ ታዳጊ ተጫዋች ሽልማትን አሸንፏል፡፡ በጀርመን አስተናጋጅነት በተካሄደው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫን ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ያሸነፈው ያማል የውድድሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማትንም አሸንፏል፡፡ በተመሳሳይ የተጫዋቹ ወኪል ጆርጌ…

 ጓርዲዮላን ምን ነካቸው?

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ስፔናዊው የእግር ኳስ ሊቅ አሰልጣኝ ፔፕ ጓርዲዮላ ከትናንቱ ጨዋታ በኋላ ጭንቅላታቸውን እና አፍንጫቸውን በጥፍራቸው መቦጫጨራቸው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ በውድድር ዓመቱ ማንቼስተር ሲቲ እያሳየ ባለው ደካማ እንቅስቃሴ ምክንያት ከተጫዋቹ ጋር እሰጣገባ ውስጥ የገቡት አሰልጣኙ÷ በተከታታይ ነጥብ መጣላቸውን ተከትሎ የሥነ ልቦና ጫና…

በሻምፒየንስ ሊጉ ሊቨርፑል ከሪያል ማድሪድ የሚያድርጉት ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ 5ኛ ዙር ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ቀጥለው ሲካሄዱ ሊቨርፑል እና ሪያል ማድሪድ አንፊልድ ላይ የሚያደርጉት ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል፡፡ ምሽት 2 ሠዓት ከ45 ላይ የሰርቢያው ሬድ ስታር ቤልግሬድ ከጀርመኑ ስቱትጋርት እንዲሁም የኦትስሪያው ስትሩም ግራዝ ከስፔኑ ዢሮና ይጫወታሉ፡፡…