ስፓርት
ማንቸስተር ሲቲ የሊጉ መሪ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 9ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ማንቸስተር ሲቲና ብሬንትፎርድ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
ቀን 11 ሰዓት ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች ማንቸስተር ሲቲ ሳውዝአምፕተንን 1ለ0 በሆነ ጠባብ ውጤት ሲያሸንፍ ብሬንትፎርድ ደግሞ ኢፕስዊች ታውንን 4ለ3 ረትቷል፡፡
አስቶንቪላ ከቦርንሞውዝ 1ለ1 እንዲሁም ብራይተን ከዎልቭስ 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ አንድ ጨዋታ ከሚቀረው ሊቨርፑል የሊጉን መሪነት ተረክቧል፡፡
Read More...
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 9ኛ ሳምንት ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 9ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብሮች በዛሬው እለት ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡
ቀን 11 ሰዓት ላይ በሊጉ ሰንጠረዥ በ20 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቸስተር ሲቲ በሜዳው ኢቲሃድ ሳውዝአምፕተንን ያስተናግዳል።
በተመሳሳይ ሰዓት አስቶንቪላ ከቦርንሞውዝ፣ ብሬንትፎርድ ከኢፕስዊች ታውን፣ ብራይተን…
አሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ በተጫዋችነትና አሰልጣኝነት ለረጅም ዓመታት ያገለገለው አስራት ሃይሌ (ጎራዴው) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
አሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ማረፉ ተሰምቷል።
አሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ውጣ ውረድን አልፎ በርካታ ድልን በተጫዋችነትና በአሰልጣኝነት የተቀዳጀ ጠንካራ…
የአትሌት መዲና የ5 ሺህ ሜትር ውጤት በክብረ-ወሰንነት ፀደቀ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) - በኢትዮጵያዊቷ አትሌት መዲና ኢሳ ከ20 ዓመት በታች የ5000 ሜትር የሴቶች የሩጫ ውድድር የተመዘገበው ውጤት በክብረ-ወሰንነት ፀደቀ፡፡
ባለፈው ወር በቤልጂየም ብራስልስ በተካሄደው ሩጫ የ19 ዓመቷ አትሌት መዲና በ14 ደቂቃ ከ21 ሰከንድ 89 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ውድድሩን ማጠናቀቋ ይታወሳል፡፡
በአትሌት ጥሩነሽ…
በፕሪሚየር ሊጉ መቐለ 70 እንደርታ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ)በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቐለ 70 እንደርታ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ 5ተኛ ሳምንት መርሐ ግብር በድሬዳዋ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መቐለ 70 እንደርታ እናከድሬዳዋ ከተማ ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
የመቐለ 70 እንደርታ የማሸነፊያ ሁለት ጎሎችን ያሬድ ብርሃኑ ሲያስቆጥር አሸናፊ ሐፍቱ…
አቡበከር ናስር ሱፐር ስፖርት ዩናትድን ተቀላቀለ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በማሜሎዲ ሰንዳውንስ ሲጫዎት የነበረው አቡበከር ናስር ሌላኛውን የደቡብ አፍሪካ ክለብ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድን ተቀላቅሏል፡፡
የፊት መስመር አጥቂው በማሜሎዲ ሰንዳውንስ ቆታው ባጋጠመው ከበድ ያለ ጉዳት ምክንያት በክለቡ ያልተሳካ ገዜ መሳላፉ የሚታወስ ነው፡፡
አቡበከር በሰንዳውንስ አለመፈለጉን ተከትሎ ሱፐር ስፖርት…
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማስተናገድ አቅም አላት – የካፍ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2029 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ የማስተናገድ አቅም እንዳላት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የቀድሞው የቦትስዋና እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ማክሊን ኮርቴዝ ሌትሺዊቲ ገለጹ።
46ኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ትናንት…