ስፓርት
ኢትዮጵያ መድን ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ መድን ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ዛሬ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ የሊጉ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ብሩክ ሙሉጌታ ባስቆጠራት ግብ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
Read More...
ፋሲል ከነማ እና ባህርዳር ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ እና ባህርዳር ከተማን ያገናኛኘው የወንድማማቾች ደርቢ ባዶ ለባዶ በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቀቀ፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው የ24ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ተመጣጣኝ የጨዋታ እንቅስቃሴን አስተናግዷል።
ክለቦቹ በሊጉ 10 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ 7 ጊዜ በአቻ ውጤት…
በሻምፒየንስ ሊጉ ከሪያል ማድሪድና ባየርሙኒክ ለፍጻሜ አላፊው ዛሬ ይለያል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ለፍፃሜ ለማለፍ በሚካሄደው የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ እና ባየርንሙኒክ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ጨዋታው ምሽት 4 ሠዓት ላይ በሪያል ማድሪድ ሜዳ ሳንትያጎ ቤርናቢዩ የሚከናወን ይሆናል፡፡
በመጀመሪያው ዙር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በባየርሙኒክ ሜዳ አሊያንዝ አሬና ስታዲየም 2…
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ለፍጻሜ ለማለፍ ዛሬ ተጠባቂ ጨዋታ ይደረጋል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ለፍፃሜ ለማለፍ በሚካሄደው የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ የፈረንሳዩ ፓሪስ ሴን ዠርሜ (ፒ ኤ ሲ ጂ) እና የጀርመኑ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ጨዋታው ምሽት 4 ሠዓት ላይ በፒ ኤስ ጂ ሜዳ ፓርክ ዴስ ፕሪንስ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ባለፈው ሳምንት የተካሄደውን የመጀመሪያ…
ቅዱስ ጊዮርጊስ የዋናው ቡድን ዋና አሠልጣኝ አገደ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ የዋናው ቡድን ዋና አሠልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታን ከማሰልጠን ተግባራቸው በጊዜዊነት አግዷል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የዋናውን ቡድን እንቅስቃሴ ገምግሟል፡፡
በዚህም አሠልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ የዋናው ቡድን ዋና…
ጁለን ሎፔቴጉይ የዌስትሃም አሰልጣኝ ለመሆን ተስማሙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ጁለን ሎፔቴጉይ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ የዌስትሃም ዩናይትድ አሰልጣኝ ለመሆን ተስማምተዋል፡፡
ስምምነቱ ተፈጻሚ ከሆነም የ57 ዓመቱ የቀድሞ የዎልቭስ አሰልጣኝ በድጋሚ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ እንደሚመለሱ ይጠበቃል፡፡
የመዶሻዎቹ አለቃ ዴቪድ ሞይስ ዌስትሃም ባለፉት 9 ጨዋታዎች አንድ ጊዜ ብቻ ማሸንፉ እና…
በፕራግ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቼክ ሪፐብሊክ በተደረገ የፕራግ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ።
በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2፡08፡45 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ፤ በውድድሩ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሄርጳሳ ነጋሳ እና አባይነህ ደጉ አምስተኛ እና ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን…