ስፓርት
የፕሪሚየር ሊጉ 4ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከነገ ጀምሮ ይቀጥላል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከእረፍት መልስ ከነገ ጀምሮ በድሬዳዋ ስታዲየም በሚደረጉ ጨዋታዎች ይቀጥላል፡፡
በዚሁ መሠረት ነገ 10 ሠዓት ላይ ሀዲያ ሆሳዕና ከሐዋሳ ከተማ እና ምሽት 1 ሠዓት ላይ መቐለ 70 እንደርታ ከመቻል የሚጫወቱ ይሆናል፡፡
እንዲሁም ከነገ በስቲያ 10 ሠዓት ላይ ስሑል ሽረ ከድሬዳዋ ከተማ ሲጫወቱ በዚሁ ዕለት ምሽት 1 ሠዓት ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ጋር ይፋለማሉ፡፡
የ4ኛ ሣምንት መርሐ-ግብር ሲቀጥል…
Read More...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማምሻውን አዲስ አበባ ገብቷል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጊኒ ጋር የነበረበትን የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ በሽንፈት ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማምሻውን አዲስ አበባ ገብቷል፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ ከጊኒ አቻው ጋር ያደረጋቸውን ጨዋታቸው በደርሶ መልስ 7 ለ 1 መሸነፉ ይታወቃል፡፡
በነገው ዕለትም ቡድኑ ከጊኒ ጋር ባደረጋቸው ጨዋታዎች እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ…
ቶማስ ቱኸል የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ጀርመናዊው አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ተሾመዋል፡፡
የቀድሞ የባየርን ሙኒክ እና ቼልሲ አሰልጣኝ የእንግሊዝ ሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን እስከ ፈረንጆቹ 2026 የሚያቆያቸውን ኮንትራት ለመፈረም ከእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር ጋር መስማማታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ስምምነቱን ተከትሎም…
ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከማንቼስተር ዩናይትድ አምባሳደርነት ሊነሱ ነው
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞው ስኬታማ አሰልጣኝና ባለፉት ዓመታት የቡድኑ ዓለም አቀፍ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በዓመቱ መጨረሻ ከኃላፊነታቸው እንደሚሰናበቱ ተሰምቷል፡፡
ሰር አሌክስ ከፈረንጆቹ 2013 ጀምሮ ቀያይ ሰይጣኖቹን በዓለም አቀፍ አምባሳደርነት እንዲሁም ክለቡን በዳይሬክተርነት በማገልገላቸው…
በቺካጎ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ቺካጎ በተካሄደው "ቺካጎ ማራቶን 2024 "የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡
በወንዶች ማራቶን ውድድር ኬንያዊው አትሌት ጆን ኬሪ 2 ሰዓት ከ2 ደቂቃ ከ42 ሴኮንድ በመግባት በ1ኛነት ሲያጠናቅቅ ኢትዮጵያዊው መሐመድ ኢሳ ደግሞ በ2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ39 ሴኮንድ…
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ጨዋታውን ያደርጋል
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ምሽት 1 ሰዓት ላይ በአቢጃን ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ለዚህም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አስቀድሞ ወደ ኮትዲቯር አቢጃን የተጓዘ ሲሆን÷ለዛሬው ጨዋታ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱ ተጠቁሟል፡፡
በጨዋታው አማካዩ ቢኒያም በላይ በጉዳት ከመጨረሻዎቹ ልምምድ ውጭ መሆኑ…
ከ4ኛ እስከ 13ኛ ሳምንት ያሉት የፕሪሚየርሊጉ ጨዋታዎች ማስተካከያ ተደረገባቸው
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 1፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ4ኛ እስከ 13ኛ ሳምንት ባሉ መርሐ-ግብሮች የኢትዮጵያ ፕሪሚር ሊግ ጨዋታዎች ላይ ማስተካከያ መደረጉን የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ አክሲዮን ማኅበር አስታወቀ፡፡
የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ሳምንት መርሐ-ግብሮች በድሬዳዋ ስታዲየም ከተደረጉ በኋላ በብሔራዊ ቡድኑ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ምክንያት…