Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ስታዲየም ይጀመራል። በዚህ መሰረትም መቐለ 70 እንደርታ እና ሃዲያ ሆሳዕና ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም የሊጉን የመክፈቻ ጨዋታ ያካሂዳሉ፡፡ የሊጉ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብ ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት ላይ አርባ ምንጭ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ ይጫወታሉ። በነገው ዕለት ደግሞ ወልቂጤ ከተማ ከመቻል ከቀኑ 10 ሰዓት እንዲሁም ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከባህር ዳር ከተማ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን…
Read More...

የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኮከቦች ሽልማት መርሐ ግብር ተከናወነ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኮከቦች ሽልማት እና የማጠቃለያ መርሐ ግብር በድሬደዋ ከተማ ተካሂዷል። በዕለቱ በ7 ዘርፍ የዓመቱ ኮከቦች የተሸለሙ ሲሆን ፥ ለተሳታፊ ክለቦች እና ባለሜዳዎች የገንዘብ ክፍፍል ተደርጓል። በዚህ መሰረትም የውድድር አዘጋጅ ባለሜዳዎች አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ 4 ሚሊየን…

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ለተሳተፉ አትሌቶች የዕዉቅናና ሽልማት መርሐ-ግብር አካሄደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ለተሳተፉ አትሌቶች የዕውቅና እና የሽልማት መርሐ ግብር አካሄደ። ታምራት ቶላ በማራቶን ብቸኛ ወርቅ በማስገኘቱ 2 ሚሊየን ብር ሲሸለም፥ በውድድሩ የብር ሜዳሊያ ያስገኙት ትዕግሥት አሰፋ፣ ፅጌ ድጉማና በሪሁ አረጋዊ እያንዳንዳቸው 1 ሚሊየን ብር ተበርክቶላቸዋል።…

ሮማ አሰልጣኝ ዳንዔል ዲ ሮሲን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የጣሊያኑ ክለብ ሮማ አሰልጣኝ ዳንዔል ዲ ሮሲን ከኃላፊነታቸው ማንሳቱን አስታውቋል፡፡ አሰልጣኙ ከኃላፊነታቸው የተነሱት ሮማን ስኬታማ ማድረግ አልቻሉም በሚል ነው፡፡ ከአደረጓቸው አራት ጨዋታዎች ሦስቱን በአቻ አንዱን በሽንፈት ማጠናቀቃቸውም ዲ ሮሲ እንዲሰናበቱ አድርጓል ተብሏል፡፡ እስከ አሁን ያለውን ውጤት ተከትሎም…

ብራዚላዊው ታዳጊ ኤንድሪክ በሪያል ማድሪድ መለያ በዕድሜ ትንሹ የቻምፒዮንስ ሊግ ግብ አስቆጣሪ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ብራዚላዊው ታዳጊ ኤንድሪክ ትናንት ምሽት ስቱትጋርት ላይ ግብ ማስቆጠሩን ተከትሎ በሪያል ማድሪድ ታሪክ በአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ በትንሽ ዕድሜ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ባለቤት ሆኗል፡፡ ኤንድሪክ በክረምቱ የዝውውር መስኮት የብራዚሉን ክለብ ፓልሜራስን በመልቀቅ ነጭ ለባሾቹን (ማሬንጌዎቹን) መቀላቀሉ ይታወቃል፡፡…

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ዛሬ ሲቀጥል ማንቼስተር ሲቲን ከኢንተርሚላን የሚያገናኘው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ ምሽት 1 ሠዓት ከ45 ላይ የጣሊያኑ ቦሎኛ ከዩክሬኑ ሻካታር ዶኔስክ እንዲሁም የቼክ ሪፐብሊኩ ክለብ ስፓርታ ፕራግ ከኦስትሪያው ሬድቡል ሳልዝበርግ ይገናኛሉ፡፡ በሌላ በኩል የስኮትላንዱ ሴልቲክ ከስሎቫኪያው ስሎቫክ…

ፌዴሬሽኑ ከጎፈሬ ኩባንያ ጋር የዳኞች ትጥቅ አቅርቦት ስምምነት ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና ጎፈሬ የትጥቅ አምራች ኩባንያ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የዳኞች ትጥቅ አቅርቦት የአጋርነት ስምምነት ተፈራርመዋል። በፊርማ ሥነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን፣ የጎፈሬ መስራችና ባለቤት አቶ ሳሙኤል መኮንን እንዲሁም የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ…