Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ከተማን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ ሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር 10 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አርባምንጭ ከተማ በድሬደዋ ስታዲየም ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ጎሎችን ኪቲካ ጅማ፣ አንደኛዋን ጎል ደግሞ ፉዓድ ፈረጃ ሲያስቆጥር የአርባምንጭ ከተማን ብቸኛ ጎል አህብያ ብራያን አስቆጥሯል፡፡
Read More...

የአትሌት ትዕግስት አሰፋ የማራቶን ሰዓት በጊነስ ወርልድ ተመዘገበ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ትዕግስት አሰፋ በበርሊን ማራቶን ያስመዘገበችው ሰዓት በዓለም ዓቀፉ የድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ሰፍተሯል። አትሌቷ በበርሊን የሴቶች ማራቶን 2 ሰአት ከ11 ደቂቃ ከ53 ሰከንድ በመግባት አዲስ ክብረ ወሰን ማስመዝገቧ ይታወሳል። አትሌቷ ከጊነስ ወርልድ ሪከርድ መመዝገቧን የሚገልፅ ሰርተፍኬት መቀበሏን ከባህልና…

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ጅቡቲን 5 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ከጅቡቲ ጋር ያደረገውን የአቋም መለኪያ ጨዋታ 5 ለ 0 አሸንፏል፡፡ የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ሁለተኛ የአቋም መለኪያ ጨዋታውን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከጅቡቲ አቻው ጋር አድርጓል፡፡ ይህን ጨዋታም ቸርነት መንግሥቱ (2)፣ ናትናኤል…

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና ሐዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ ስታዲየም በተደረገው 3ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር ኢትዮጵያ ቡና ሐዋሳ ከተማን 3 ለ 1 አሸነፈ:: የኢትዮጵያ ቡናን ግቦች ኮንኮኒ ሀፍዝ፣ ረምኬል ጀምስ እና ዳዊት ሽፈራው ሲያስቆጥሩ÷ ለየዋሳ ከተማን ብቸኛ ግብ አሊ ሱሌማን ከመረብ አሳርፏል፡፡ እንዲሁም መቻል ወላይታ ድቻን 3 ለ 1…

የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሰልጠኝ አሊዩ ሲሴን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አመታት የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጠኝ የነበረው አሊዩ ሲሴ መሰናበቱ ተነገረ። የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአስልጣኙ ኮንትራት በማለቁ ማሰነበቱን በመግለጽ አሰልጣኙ በብሔራዊ ቡድኑ ጋር ለነበረው ስኬት አመስግኗል፡፡ የ48 ዓመቱ አሊዩ ሲሴ በአሰልጣኝነት ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር የአፍሪካ ዋንጫን ያነሳ…

2ኛ ዙር የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ቀጥለው ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ 2ኛ ዙር የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ቀጥለው ሲደረጉ የእንግሊዙ አስቶንቪላ ከረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ ባየርን ሙኒክን ይገጥማል፡፡ ምሽት 1 ሰዓት ከ45 ላይ የስፔኑ ዢሮና ከኔዘርላንድሱ ፌይኑርድ እንዲሁም ሻካታር ዶኔስክ ከአትላንታ ይጫወታሉ፡፡ በሌላ ጨዋታ መርሐ-ግብር ምሽት 4 ሰዓት…

በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ እና ስሑል ሽረ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ እና ስሑል ሽረ አቻ ተለያይተዋል፡፡ ፋሲል ከነማ እና ስሑል ሽረ 10 ሠዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ጨዋታቸውን አድርገው 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ የዕለቱ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት ላይ ባህርዳር ከተማ እና…