ስፓርት
500 ስፖርተኞች የሚሳተፉበት የክለቦች ሻምፒዮና ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ የወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን የ2015 ዓ.ም የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በአራት ኪሎ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ተጀምሯል።
በሻምፒዮና ውድድሩ 45 ክለቦች በ12 የኪሎ ካታጎሪ በሁለቱም ጾታ ይወዳደራሉ፡፡
በአጠቃላይ 500 ስፖርተኞች በውድድሩ እንደሚሳተፉ አዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
የ2015 ዓ.ም የአዲስ አበባ የወርልድ ቴኳንዶ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ሐምሌ 5 ቀን 2015ዓ.ም ፍፃሜውን ያገኛል።
Read More...
ቅዱስ ጊዮርጊስና ድሬዳዋ ከተማ ያደረጉት የሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት እና የሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡
ድሬዳዋ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስን ያገናኘው የሊጉ የመጨረሻ ጨዋት 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡
የድሬዳዋ ከተማን ግብ አጥቂው ቢኒያም ጌታቸው ሲያስቆጥር÷ቅዱስ ጊዮርጊስን አቻ…
ፋሲል ከነማ ተጫዋቾች እንዳያዘዋውር ታገደ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 1 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ከስምንት ቀናት በኋላ በሚከፈተው የዝውውር መስኮት ተጫዋች እንዳያስፈርሙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴ ውሳኔ አሳልፏል።
ክለቡ የታገደው ከቀድሞ አሰልጣኙ ኃይሉ ነጋሽ የደመወዝ ክፍያ ጋር በተያያዘ የተወሰነበትን ውሳኔ ተፈጻሚ ባለማድረጉ መሆኑን ሶከር ኢትዮጵያ አስነብቧል።…
ባህርዳር ከተማ እና ሀዲያ ሆሳዕና የመጨረሻ ጨዋታቸውን በድል አጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል።
ቀደም ብሎ ከወላይታ ዲቻ ጋር የተጫወቱት የጣና ሞገዶቹ ባህር ዳር ከተማ በአደም አባስ ብቸኛ ጎል 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ባህርዳር ከተማ ነጥቡን 60 በማድረስ በሊጉ 2ኛ…
የፊታችን ሐምሌ 8 ቀን የኢትዮጵያ የፕሪሚየር ሊግ ተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ይከፈታል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከፊታችን ሐምሌ 8 ቀን ጀምሮ የኢትዮጵያ ወንዶች እና ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተጫዋቾች የዝውውር መስኮት እንደሚከፈት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡
የዝውውር መስኮቱ ከሐምሌ 8 ቀን እስከ መስከረም 25 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ተገልጿል፡፡
የተጫዋቾች ዝውውር ሕጋዊነት የሚፀድቀውም÷ በኢትዮጵያ እግር ኳስ…
አርባ ምንጭ ከተማ ወደ ታችኛው ሊግ ወርዷል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አርባ ምንጭ ከተማ ወደ ታችኛው ሊግ የወረደ ሶስተኛው ቡድን ሆኗል፡፡
አርባ ምንጭ ከተማ እና ሃዋሳ ከተማ በዛሬው ዕለት ያደረጉት ጨዋታ በአንድ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም አርባ ምንጭ ከተማ በ34 ነጥብ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን የወረደ ሲሆን÷ በአንጻሩ ወልቂጤ ከነማ ከመውረድ…
የአዲስ አበባ ስታዲየም በመጪው ዓመት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ማስተናገድ እንደሚጀምር ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ስታዲየም በመጪው ዓመት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ማስተናገድ እንደሚጀምር የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ የአዲስ አበባ ስታዲየም የግንባታ ሒደትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንደገለፁት÷በ2013 ዓ.ም የእድሳት ስራው የተጀመረው የአዲስ…