Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ብርቄ ኃየሎም እና ድርቤ ወልተጂ በ1 ሺህ 500 ሜትር ለፍፃሜ አለፉ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀንጋሪ ቡዳፔስት 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አትሌት ብርቄ ኃየሎም እና ድርቤ ወልተጂ በ1 ሺህ 500 ሜትር ወደ ፍፃሜ አለፉ፡፡ አትሌት ብርቄ ኃየሎም ርቀቱን በ4 ደቂቃ ከ02 ሰከንድ ከ46 ማይክሮ ሰከንድ 2ኛ በመውጣት ወደ ፍፃሜ ማለፏን ስታረጋግጥ በተመሳሳይ ከምድብ ሁለት ድርቤ ወልተጂም 3 ደቂቃ ከ55 ሰከንድ ከ18 ማይክሮ ሰከንድ በመግባትና 2ኛ በመውጣት ወደ ፍፃሜ ማለፍ ችላለች ፡፡ አትሌት ሂሩት መሸሻ 9ኛ በመውጣት ወደሚቀጥለው ዙር ማለፍ አልቻለችም፡፡
Read More...

ስፔን የ2023 የሴቶች የዓለም ዋንጫን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2023 የሴቶች የዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን እንግሊዝን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን አንስታለች። የቡድኑ አምበል ኦልጋ ካርሞና በ29ኛው ደቂቃ ለስፔን የማሸነፊያዋን ጎል አስቆጥራለች። የእንግሊዟ ግብ ጠባቂ ሜሪ ኢርፕስ በሁለተኛው አጋማሽ የጄኒፈር ሄርሞሶን ፍፁም ቅጣት ምት አድናለች።…

ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁበት የፍጻሜ ውድድር ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁበት የ10 ሺህ ሜትር ወንዶች ፍጻሜ ውድድር ምሽት 1፡25 ላይ ይካሄዳል፡፡ በውድድሩ÷ አትሌት በሪሁ አረጋዊ፣ ሰለሞን ባረጋ እና ይስማው ድሉ ተጠባቂ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ቀን 12፡05 ላይ በሚካሄደው የሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር የግማሽ ፍጻሜ ውድድር÷ አትሌት ሂሩት መሸሻ፣ ድርቤ ወልተጂ…

ባሕርዳር ከተማ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን ከአዛም ጋር ያደርጋል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በካፍ የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ባሕርዳር ከተማ የመጀመሪያ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን ዛሬ ከታንዛንያው አዛም ክለብ ጋር ያካሂዳል። ጨዋታው ከቀኑ 10 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይከናወናል። በአሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው የሚሰለጥነው ባሕርዳር ከተማ÷ ለጨዋታው በባሕርዳር እና አዲስ አበባ ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል።…

ኢትዮጵያ በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሩጫ የወርቅ፣ ብርና ነሐስ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡዳፔስት የአለም  የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያዊያን ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት የወርቅ፣ የብርና የነሃስ ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው አስገኙ። በሀንጋሪ እየተካሄደ ባለው  የ19ኛው የአለም  የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በመጀመሪያው ቀን የ10 ሺህ ሜትር ሴቶች የፍፃሜ ውድድር ተካሂዷል። በውድድሩም ጉዳፍ ፀጋይ 1ኛ፣ ለተሰንበት…

ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ለተሰጣት እውቅና የእንኳን ደስ ያለሽ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በሃንጋሪ ቡዳፔስት በተካሄደው 54ኛው የዓለም አትሌቲክስ ጉባዔ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በአትሌቲክሱ ዘርፍ ላበረከተችው አስተዋጽኦ ለተሰጣት የ”ፕላክ ኦፍ ሜሪት” እውቅና የእንኳን ደስ ያለሽ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዚዳንቷ በመልዕክታቸው÷…

ዛሬ ምሽት በሴቶች 10 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይጠበቃሉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሃንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ በሚገኘው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ምሽት በሚካሄደው የሴቶች 10 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለአሸናፊነትከፍተኛ ግምት ተሰጥቷቸዋል። በውድድሩ በአሜሪካ ኦሬጎን በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በርቀቱ የወርቅ ሜዳሊያ ያገኘችው አትሌት ለተሰንበት…