Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ዛሬ ወደ ውድድር ትመለሳለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የረጅም ርቀት ሯጯ ጥሩነሽ ዲባባ ከአራት ዓመታት በኋላ ዛሬ በአሜሪካ በሚካሄደው የሂውስተን ግማሽ ማራቶን ወደ ውድድር ትመለሳለች። የሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ እና የአምስት ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነችው አትሌት ጥሩነሽ ባለፉት አራት ዓመት ምንም አይነት ውድድር አድርጋ አታውቅም። ዛሬ ለ22ኛ ጊዜ በሚካሄደው የሂውስተን ማራቶን ከሚሳተፉ አትሌቶች መካከል ጥሩነሽ ዲባባ ትገኝበታለች። አትሌት ጥሩነሽ በርቀቱ ያስመዘገበችው ፈጣን ሰዓት በፈረንጆቹ በ2017 በተባበሩት አረብ…
Read More...

በሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ማለዳ በሕንድ በተካሄደው የሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ። በሴቶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 8ኛ ተከታትለው በመግባት በበላይት አጠናቀዋል፡፡ በውድድሩ አትሌት አንቺዓለም ሃይማኖት 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር…

በማንችስተር ደርቢ ዩናይትድ ሲቲን 2 ለ1 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ የማንችስተር ደርቢ ማንችስተር ዩናይትድ ማንችስተር ሲቲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ማስመዝገብ ችሏል። የማንችስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ማርከስ ራሽፎርድ እና ፈርናንዴዝ ሲያስቆጥሩ የማንችስተር ሲቲን ግብ ግሪሊሽ አስቆጥሯል። ማንችስተር ዩናይትድ በተከታታይ…

ኢትዮጵያ ከሞዛምቢክ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ ያለምንም ግብ አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ7ኛው የአፍሪካ ሀገራት ቻምፒየን ሺፕ ቻን ውድድር የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ከሞዛምቢክ ጋር ያደረገችው ኢትዮጵያ ጨዋታዋን ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት አጠናቃለች። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አቻ መውጣቱን ተከትሎ አንድ ነጥብ በመያዝ በምድቡ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። 7ኛው የአፍሪካ ሀገራት ቻምፒየንሺፕ ውድድር…

ፊፋ የአርጀንቲና ብሄራዊ ቡድን በአለም ዋንጫ ስላሳየው ያልተገባ ባህሪ ምርመራ እንደሚያደርግ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ባለፈው ወር በኳታር በተካሄደው የአለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ፥ የ2018 ዓለም ዋንጫ አሸናፊዋን ፈረንሳይን በፍፁም ቅጣት ምት አሸንፋ ዋንጫውን ለሶስተኛ ጊዜ ባነሳችው በአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን "ያልተገባ ባህሪ" ላይ የዲሲፕሊን ሂደቶችን ከፍቻለሁ ብሏል። በፍፃሜ ጨዋታው መጨረሻ ግብ…

ኢትዮጵያ የፊታችን እሑድ የምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ሪጅን ጉባኤን ታስተናግዳለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 10 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተካለሉበት የአትሌቲክስ ሪጅን ጉባኤ የፊታችን እሑድ ጥር 7 ቀን 2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ይካሄዳል፡፡ በጉባኤው የሪጅኑ ፕሬዚዳንት፣ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንት፣ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫና በሪጅኑ የኮንፌዴሬሽን ኦፎ አፍሪካ አትሌቲክስ ካውንስል አባላት ውክልና…

ብሄራዊ ቡድኑ ከሞዛምቢክ ጋር ለመጫዎት ዝግጁ ነው – አሰልጣኝ ውበቱ አባተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብሄራዊ ቡድኑ በነገው ዕለት ከሞዛምቢክ ጋር ለሚደርገው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተናገሩ፡፡ በነገው ዕለት የሚካሄደውን ጨዋታ አስመልክቶ የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና አምበሉ መስኡድ መሐመድ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። አሰልጣኙ በመግለጫቸውም÷ ብሄራዊ ቡድኑ በሀገር ቤት ዝግጅት ሲያደርግ…