Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አርሰናል ብራይተንን በማሸነፍ ሊጉን መምራት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አርሰናል ብራይተንን 2 ለ 0 በማሸነፍ ፕሪሚየር ሊጉን በጊዜያዊነት ከሊቨርፑል ተረክቦ መምራት ጀምሯል፡፡ በኤሚሬትስ ስታዲየም ብራይተንን ያስተናገዱት መድፈኞቹ በጋብሬል ጄሱስ እና ካይ ሀቨርትዝ ጎሎች 2 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም÷ መድፈኞቹ ነጥባቸውን 39 በማድረስ የፕሪሚርሊጉን መሪነት በጊዜያዊነት ከሊቨርፑል ተረክበዋል፡፡ በሌላ ጨዋታ  ዌስትሃም ዎልቭስን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ፤ የኡናይ ኤሚሬው ቡድን አስቶንቪላ ከመመራት ተነስቶ 2 ለ 1 በማሸነፍ በ38 ነጥቦች 2ኛ ደረጃ ላይ…
Read More...

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና ድል ቀናው

አዲስ አበባ፣ ታኅሳስ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን 4 ለ1 አሸንፏል፡፡ የሲዳማ ቡናን ጎሎችም÷ በዛብህ መለዮ፣ ሀብታሙ ገዛኸኝ፣ ማይክል ኪፕሮል እና ቡልቻ ሹራ አስቆጥረዋል፡፡ የወላይታ ድቻን ብቸኛ ጎል ደግሞ ዮናታን ኤልያስ በሁለተኛው አጋማሽ ማስቆጠር ችሏል፡፡ ሲዳማ ቡና ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን ስምንት በማድረስ…

በሕንድ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕንድ በተካሄደ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በሕንድ ኮልካታ ከተማ የተካሄደውን የ25 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡ አትሌቷ ርቀቱን 1ሰዓት 18 ደቂቃ ከ47 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ቀዳሚ የሆነቸው ፡፡…

ቼልሲና ኒውካስል ዩናይትድ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየም ሊግ በሜዳቸው የተጫወቱት ቼልሲና ኒውካስል ዩናይትድ ድል ቀናቸው። በሜዳው ሼፊልድ ዩናይትድን ያስተናገደው ቼልሲ በፓልመርና መጃክሰን አማካኝነት በ54ኛውና በ61ኛው ደቂቃ ባስቆጠራቸው ግቦች 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏን። ፉልሃምን ያስተናገደው ኒውካስል ዩናይትድ 3 ለ 0 ሲያሸንፍ…

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ኢትዮጵያ መድን ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 8ኛ ሳምንት በዛሬው እለት ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ መጀመሪያ 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 አሸንፏል። አዲስ ግደይ እና ባሲሩ ኡመር ለኢዮጵያ ንግድ ባንክ የማሸነፊያ ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ ዴሬክ ካኮዛ ደግሞ የኢትዮጵያ ቡናን ጎል…

በፕሪሚየር ሊጉ ሀድያ ሆሳዕና እና ባህር ዳር ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 5 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 8ኛ ሳምንት ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል።   ከሰአት በኋላ በተካሄደ ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ተገናኝተው ሀድያ ሆሳዕና 2 ለ 1 አሸንፏል።   ተመስገን ብርሃኑ እና ግርማ በቀለ ለሀድያ ሆሳዕና የድል ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ ፍቃዱ አለሙ ደግሞ ለፋሲል ከነማ…

የአንካራጉቹ እግርኳስ ቡድን ፕሬዚዳንት ፋሩክ ኮቻ ከእግር ኳስ ታገደ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጨዋታ ዳኛ በመደብደብ አስነዋሪ ተግባር የፈፀመው የቱርኩ ኤም ኬ ኢ አንካራጉቹ እግርኳስ ክለብ ፕሬዚዳንት ፋሩክ ኮቻ ከእግር በቋሚነት መታገዳቸውን የቱርክ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ባለፈው ቅዳሜ ኤም ኬ ኢ አንካራጉቹ ከችኩር ሪዘርፖር ባደረጉት ጨዋታ የእለቱ ዋና ዳኛ ሃሊል ኡሙት ሜለር…