Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ 5 ሺህ ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ በ5 ሺህ ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ አሸንፏል፡፡ በወንዶች ምድብ በተካሄደው 5 ሺህ ሜትር የፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ሰለሞን ባረጋ ርቀቱን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ÷ሙክታር እድሪስ ደግሞ 3ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡ በምድቡ አዲሱ ይሁኔ 5ኛ ሆኖ ውድድሩን የጨረሰ መሆኑንም ከአትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
Read More...

በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልቂጤ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ27ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ረፋድ ላይ በባህር ዳር አለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ከነዓን ማርክነህ በ25ኛ ደቂቃ እንዲሁም ጋቶች ፓኖም በ79ኛ ደቂቃ የቅዱስ ጊዮርጊስን የአሸናፊነት ግብ አስቆጥረዋል፡፡ ከሰዓት 10 ሰዓት ሀዋሳ ከተማ…

በኦስሎ የ5 ሺህ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀዋል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦስሎ ከተማ በ5ሺህ ሜትር የተካሄደውን የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች በበላይነት አጠናቀዋል፡፡ በወንዶች ምድብ በተካሄደው 5 ሺህ ሜትር የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ጥላሁን ሃይሌ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ÷ ሳሙኤል ተፈራ እና ጌትነት ዋሌ 2ኛ እና 3ኛ ሆኖ በመግባት ውድድሩን…

ግብፅ በኢትዮጵያ ከገጠማት መራር ሽንፈት በኋላ አሰልጣኟን አሰናበተች

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 9 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብፅ እግር ኳስ ማህበር የብሄራዊ ቡድኑን አሰልጣኝ ኢሀብ ጋላልን ከአሰልጣኝነት አሰናበተ። ግብጽ የዛሬ ሳምንት ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዋን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከጨዋታ ብልጫ ጋር 2 ለ 0 መሸነፏ ይታወሳል። ከዚህ ባለፈም በወዳጅነት ጨዋታ ከትናንት በስትያ በደቡብ ኮሪያ የ4 ለ 1 ሽንፈት…

በፕሪሚየር ሊጉ ጅማ አባ ጅፋር እና ፋሲል ከነማ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጅማ አባ ጅፋር ሃድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ አንጋፋው ዳዊት እስጢፋኖስ ከረጅም ጊዜ በኋላ ባስቆጠራት ጎል ጅማ አባ ጅፋር ሙሉ ሶስት ነጥብ ማግኘት ችሏል፡፡ በ23 ነጥብ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው ጅማ አባ ጅፋር የዛሬው ድል…

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ሰኔ 8፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ በባህርዳር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አዳማ ከተማ እስከ እረፍት በአሜ መሀመድ ብቸናኛ ጎል ሲመራ ቢቆይም ከዕረፍት መልስ አቡበከር ናስር ያስቆጠራቸው ጎሎች ቡናማዎችን አሸናፊ አድርገዋል፡፡ ኢትዮጵያ ቡና ማሸነፉን ተከትሎ…

ከዕረፍት በተመለሰው ፕሪሚየር ሊግ አርባ ምንጭ ከተማ ድል ቀንቶታል

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከዕረፍት መልስ ዛሬ ተካሂዷል። ረፋድ ላይ ሲዳማ ቡናን ከአርባ ምንጭ ከተማ ባገናኘው ጨዋታ አርባ ምንጭ አሸናፊ ሆኗል። ጨዋታው 2 ለ 1 ሲጠናቀቅ ኤሪክ ካፓይቶ ሁለቱን የማሸነፊያ ጎሎች ለአርባ ምንጭ ከተማ አስቆጥሯል። የሲዳማ ቡና ማስተዛዘኛ ጎል ደግሞ…