ስፓርት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ ታንዛንያ አቀና
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዛሬው ዕለት ወደ ታንዛንያ አቅንቷል፡፡
ዋልያዎቹ በአገር ውስጥ ሊግ የሚገኙ ተጫዋቾች ብቻ በሚሳተፉበት የአፍሪካ እግር ኳስ ሻምፒዮና (ቻን) ጨዋታ ከሩዋንዳ አቻቸው ጋር የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታቸውን ለማድረግ ነው ወደ ታንዛንያ ያመሩት፡፡
ሰባተኛው የቻን የእግር ኳስ ውድድር በጥር እና የካቲት ወር 2015 ዓ.ም በአልጄሪያ አስተናጋጅነት ይካሄዳል።
ዋልያዎቹ በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ነሐሴ 20 እና 29 ቀን 2014 ዓ.ም ከሩዋንዳ አቻው ጋር ጨዋታቸውን…
Read More...
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የምስጋና መርሐ ግብር አካሄደ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በ2014 በጀት ዓመት ለነበረው ውጤታማ ጊዜ ከጎኑ ለነበሩ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት የምስጋና መርሐ ግብር አካሄደ፡፡
በመርሐ ግብሩ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጀላ መርዳሳ ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታዎች አምባሳደር መስፍን ቸርነት እና ወ/ሮ ወርቅነሽ ብሩ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ…
በብራዚል እና አርጀንቲና የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው
በብራዚል እና አርጀንቲና በተካሄዱ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በብራዚል ሪዮ ዲ ጄኔሮ እና በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄዱ የግማሽ ማራቶን ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በወንዶች የግማሽ ማራቶን ውድድር አሰፋ በቀለ በ1 ሠዓት ከ3 ደቂቃ ከ52 ሠከንድ በመግባት ቀዳሚ በመሆን…
ኦሮሚያ ክልል እና ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሻምፒዮን ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኦሮሚያ ክልል እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ክልሎች እና ክለቦች ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
በክልሎች ሻምፒዮና መካከል በተደረገ የፍጻሜ ጨዋታ ኦሮሚያ ክልል ደቡብ ክልልን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት መርታቱን ተከትሎ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
የማሸነፊያ ጎሎቹን ዮሴፍ ዳንኤል እና ጁንዲ ሃጂ…
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የኡጋንዳ አቻውን 1 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአቋም መለኪያ ጨዋታ ከኡጋንዳ አቻው ጋር የተጫወተው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የኡጋንዳ አቻውን 1 ለ 0 አሽንፏል፡፡
የብሄራዊ ቡድኑን የአሸናፊነት ጎል የፋሲል ከነማው የመሐል ተጫዋች በዛብህ መለዮ 93ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በቀጣይ እሁድ ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታቸውን እንደሚያከናውኑ…
ለእግር ኳስ ፌዴሬሽን አመራርነት የመጨረሻ እጩዎች ይፋ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምርጫ አስፈፃሚው ኮሚቴ ከታዩ በኋላ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፕሬዚዳንት እና ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የመጨረሻ እጩዎች ይፋ ሆነዋል፡፡
በዚህም መሰረት 32 የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ አባለት ለመጨረሻ እጩነት ሲቀርቡ÷ 3 እጨዎች ደግሞ ለእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንትነት የመጨረሻ እጩዎች በመሆን ቀርበዋል፡፡
ይህ…
የአፍሪካ ከ23 ዓመት በታች ማጣሪያ ድልድል ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2023 የሚካሄደው የአፍሪካ ከ23 ዓመት በታች የማጣሪያ ውድድር ድልድል ዛሬ ይፋ ሆኗል፡፡
በዚህ መሰረትም ኢትዮጵያ በመጀመሪያው ዙር የማጣሪያ ውድድር ከዴሞክራቲክ ኮንጎ ጋር ተደልድላለች።
ኢትዮጵያ ይህን ዙር የምታልፍ ከሆነ በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ አልጄሪያን የምትገጥም መሆኑን ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው…