Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በወንዶች 10 ሺህ ሜትር ኡጋንዳ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በወንዶች 10 ሺህ ሜትር ኡጋንዳ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች። ውድድሩን ኡጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቼፕቴጌ አሸንፏል። እስከ ፍፃሜው ብርቱ ፉክክር ካደረጉት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች መካከል ሰለሞን ባረጋ አምስተኛ እና በሪሁ አረጋዊ ሰባተኛ በመሆን አጠናቀዋል። ኬንያዊ እና ኡጋንዳዊ አትሌቶች በተከታታይ ሁለተኛና ሶስተኛ ሆነው ጨርሰዋል።
Read More...

የዓለም የወንዶች ማራቶን ፍጻሜ ውድድርን አትሌት ታምራት ቶላ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የወንዶች ማራቶን የፍጻሜ ውድድርን አትሌት ታምራት ቶላ አሸነፈ፡፡ አትሌት ታምራት ቶላ 2 ሰዓት ከ 5 ደቂቃ ከ 36 ሰከንድ በመግባት ነው ውድድሩን ያሸነፈው፡፡ አትሌት ሞስነት ገረመው ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድርሩን አጠናቋል፡፡ በውድድሩ…

የወንዶች ማራቶን የፍጻሜ ውድድር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የወንዶች ማራቶን የፍጻሜ ውድድር በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በውድድሩም÷ አትሌት ሌሊሳ ደሲሳ፣ አትሌት ሙስነት ገረመው፣ አትሌት ሰይፉ ቱራ እና አትሌት ታምራት ቶላ ተሳትፈዋል፡፡ በአሜሪካ ኦሪገን እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ሦስተኛ ቀኑን ይዟል፡፡…

በኦሬገን ዛሬ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶች ማራቶንና 10 ሺህ ሜትር ውድድሮች ይጠበቃሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሬገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶች ማራቶን እና 10 ሺህ ሜትር ውድድሮች ይጠበቃሉ። ቀን 10 ሰዓት ከ15 ላይ የወንዶች ማራቶን የሚካሄድ ሲሆን፥ ሌሊሳ ደሲሳ፣ ሙስነት ገረመው፣ ሰይፉ ቱራ እና ዓየለ ቶላ ይሮጣሉ። ምሽት 5 ሰዓት ላይም የወንዶች 10 ሺህ ሜትር ፍፃሜ ይካሄዳል።…

በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ1ሺህ 500 ሜትር ማጣሪያዎች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ወደ ቀጣይ ዙር አልፈዋል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሬገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለሊቱን በተካሄዱ የወንዶችና ሴቶች 1ሺህ 500 ሜትር ማጣሪያዎች በሴቶች ሁሉም ኢትዮጵያውያን ተወዳዳሪዎች አልፈዋል፡፡ ጉዳፍ ጸጋይ 4፡01.28 ከምድብ አንድ 1ኛ፣ ፍረወይኒ ኃይሉ 4፡02.28 ከምድብ አንድ 4ኛ፣ ሂሩት መሸሻ 4፡04.05 በሆነ ጊዜ ከምድብ ሁለት 2ኛ በመሆን አልፈዋል፡፡…

በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በለተሰንበት ግደይ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18ኛው የኦሬገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በሴቶች 10 ሺህ ሜትር በለተሰንበት ግደይ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች። በውድድሩ ኬንያውያን አትሌቶች ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን አጠናቀዋል። እጅጋየሁ ታየ ስድስተኛ እና ቦስና ሙላቴ ስምንተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቀዋል።

በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ከተሳተፉት ሶስት አትሌቶች ሁለቱ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፈዋል

በአዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 2ኛ ቀኑን ባስቆጠረው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ከተሳተፉት ሶስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሁለቱ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡ በመጀመሪያው ምድብ የወርቅውኃ ጌታቸው 2ኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ፍፃሜ ማለፍ ስትችል መቅደስ አበበ በሁለተኛው ምድብ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ፍጻሜ ማለፏን…