ስፓርት
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አዲስ አበባ ከአዳማ ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 17፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ20ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አዲስ አበባ ከተማ ከአዳማ ከተማ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታቸውን ያለ ግብ አጠናቀዋል፡፡
የጨዋታውን ውጤት ተከትሎ አዳማ ሃዲያ ሆሳናን በግብ ክፍያ በልጦ 9ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ሲችል÷ አዲስ አበባ ከተማ በአንፃሩ በነበረበት 14ኛ ደረጃ ላይ ተቀጧል፡፡
የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቀጥሎ…
Read More...
በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ክብረ ወሰን በማሻሻል አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ሀገራት በተካሄዱ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ውድድሮችን በበላይነት አጠናቀዋል፡፡
በዚሁ መሰረት በሀምቡርግ ማራቶን÷ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው 2 ሰዓት ከ17 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት እና የቦታውን የማራቶን ክብረወሰን…
ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ተጠባቂውን ጨዋታ ለመምራት ደቡብ አፍሪካ ገቡ
አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 14፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተስማ ተጠባቂውን የማማሎዲ ሰንዳውስን እና ፔትሮ አትሌቲኮ ጨዋታ ለመዳኘት ደቡብ አፍሪካ ገብተዋል፡፡
የ2021/22 የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ወደ ፍፃሜው እየተጠጋ ሲሆን በሳምንቱ መጨረሻ አራት ውስጥ የሚገቡ ክለቦች የሚለዩበት የሩብ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታዎች…
ማንቼስተር ዩናይትድ ኤሪክ ቴን ሃግን በሦስት ዓመት ውል ማስፈረሙን አስታወቀ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 13 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ ማንቼስተር ዩናይትድ ኤሪክ ቴን ሃግን በሶስት አመት ውል ማስፈረሙን አስታወቀ።
የ52 አመቱን አሰልጣኝ ሊራዘም በሚችል የአንድ አመት ተጨማሪ ኮንትራት ለሶስት አመታት ከሆላንዱ አያክስ አምስተርዳም ማስፈረሙን ክለቡ ይፋ አድርጓል።
የእንግሊዙ ክለብ አሰልጣኙን ማስፈረሙን ተከትሎ ለአያክስ…
የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ምድብ ማጣሪያ ድልድል በትናንትናው እለት ይፋ ሆኗል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ምድብ ማጣሪያ ድልድል በትናንትናው እለት ይፋ ሆኗል፡፡
በምድብ ማጣሪያ ድልድሉ ኢትዮጵያ በምድብ 4 ከግብፅ ፣ ጊኒ እና ማላዊ ጋር ተደልድላለች።
የማጣሪያ ጨዋታዎቹ ከመጭው ግንቦት ጀምሮ የሚደረግ መሆኑን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡…
በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሃድያ ሆሳዕና ድል ቀንቶታል
በአዲስ አበባ፣ሚያዝያ 11፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ19ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ሀድያ ሆሳዕና ኦሞድ ኡኩሪ ከረጅም ጊዜ በኋላ ባስቆጠራት ጎል እስከ ዕረፍት 1 ለ 0 መምራት ችሏል፡፡
ከዕረፍት መልስ አዳማ ከተማ በአሜ ሙሀመድ ጎል አቻ መሆን ቢችልም ራምኬ ሎክ በ 87ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል…
በፕሪምየርሊጉ ድሬዳዋ ከተማ ደረጃውን ያሻሻለበትን ውጤት አስመዘገበ
አዲስ አበባ፣ሚያዚያ 10፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በ19ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ጅማ አባ ጅፋርን 2 ለ 1 በማሸነፍ ደረጃውን አሻሸሏል፡፡
ከደቂቃዎች በፊት በተካሄደው ጨዋታ አንጋፋው ተጫዋች ጋዲሳ መብራቴ እና ሄኖክ አየለ የድሬዳዋን የአሸናፊነት ጎል ሲያሰቆጥሩ ዳዊት በፍቃዱ ብቸኛዋን የጅማ አባ ጅፋር ጎል አስቆጥሯል፡፡
የጨዋታውን…