Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ነገ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 6፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአዲስ አበባ ስታዲየም በነገው ዕለት ይጀመራል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአጭር፣ በመካከለኛ ርቀት፣ በ3 ሺህ ሜ.መሰናክል፣ በእርምጃና በሜዳ ተግባራት ከታህሳስ 7 እስከ 12 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበበ ስታዲየም ነው የሚካሄደው፡፡ በመክፈቻው እለትም የአሎሎ ውርወራ ማጣሪያና ፍፃሜ፣ የስሉስ ዝላይ ማጣሪያና ፍፃሜ፣ እንዲሁም ከ100 ሜትር እስከ 800 ሜትር የማጣሪያ ውድድሮች እንደሚካሄዱ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡…
Read More...

በሳምንቱ መጨረሻ በተካሄዱ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፍነው ቅዳሜና እሁድ በተለያዩ ሀገራት በተካሄዱ የአትሌቲክስ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል። በቻይና በተካሄደ የሼንዚን የወንዶች ማራቶን ውድድር ታደሰ ቶላ እና ተረፈ ደበላ ተክታትለው በመግባት ከአንድ እስከ ሁለተኛ ያለውን ደረጃ ሲይዙ በቀለ ሙሉነህ ሰባተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል።…

የአትሌት አበበ ቢቂላ መታሰቢያና 14ኛው የካሳማ የግማሽ ማራቶን ውድድር ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአትሌት አበበ ቢቂላ መታሰቢያና 14ኛው የካሳማ ከተማ የግማሽ ማራቶን ውድድር ተካሄደ። በውድድሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸንፈዋል። በግማሽ ማራቶን ውድድሩ በወንዶች አትሌት አብዮት አብነት እንዲሁም በሴቶች ደግሞ አትሌት እታለማሁ ስንታየሁ አሸናፊዎች ሆነዋል። ውድድሩን አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣…

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 3ኛ ሳምንት ጨታዎች በተለያዩ ከተሞች ተካሂደዋል

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 4 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 3ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ተካሂደዋል። ስሁል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ መቐለ ላይ በትግራይ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ባካሄዱት ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ባህር ዳር ከነማን ያስተናገደው ሀዋሳ ከተማ 1 ለ 0 በሆነ…

ሰበታ ከተማ ለአራት ዓመታት የሚቆይ የ18 ሚሊየን ብር የስፓንሰርሽፕ ስምምነት ከሜታ አቦ ቢራ ጋር ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 3፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በዘንድሮው ዓመት ከረጅም ጊዜ በኋላ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን የተቀላቀለው ሰበታ ከተማ ለአራት ዓመታት የሚቆይ የ18 ሚሊየን ብር የስፓንሰርሽፕ ስምምነት ከሜታ አቦ ቢራ ጋር ተፈራረመ፡፡ የስፓንሰርሽፕ ስምምነቱ በትናትናው ዕለት የክለቡ የበላይ ጠባቂ እና የሰበታ ከተማ ከንቲባ አቶ ብርሃኑ በቀለ እና የክለቡ…

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሲጠቀምበት የነበረውን አርማ አሻሻለ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 29 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለረዥም አመታት ሲጠቀምበት የነበረውን አርማ አሻሻለ። ትናንት 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ያካሄደው ፌዴሬሽኑ በጉባኤው ፌዴሬሽኑን አይገልጽም እንዲሁም አላስፈላጊ ምልክቶች ተካተውበታል በሚል ቅሬታ ሲቀርብበት የቆየውን አርማ አሻሽሏል። በዚህም በአርማው መካከል የነበረው…

ሩሲያ ለ4 ዓመት ከሁሉም ስፖርታዊ ውድድሮች ታገደች

አዲስ አበባ፣ ህዳር 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሩሲያ ለ4 ዓመት በሁሉም ስፖርታዊ ውድድርች እንዳትሳተፍ ማገዱን የዓለም አቀፍ ፀረ አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ(ዋዳ) አስታውቋል። የዋዳ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በስዊዘር ላንድ ባካሄደው ስብሰባ ነው ሩሲያ ለአራት ዓመታት በማንኛውም ስፓርታዊ ውድድር እንዳትሳተፍ ውሳኔ ያስተላለፈው። ኮሚቴው ውሳኔውን ያሳለፈውም በሀገሪቱ…