ስፓርት
በጀርመን በተካሄደው የአዲዳስ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዛሬው ዕለት በጀርመን በተካሄደው የአዲዳስ አዲዜሮ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ተቀዳጅተዋል።
በ5 ኪሎ ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት መዲና ኢሳ ስታሸንፍ÷ በወንዶቹ ዮሚፍ ቀጀልቻ በቀዳሚነት አጠናቀዋል።
ከፍተኛ ፉክክር በተደረገበት የሴቶች 5 ኪሎ ሜትር ውድድር የሁለት ዓመታት አሸናፊዋ አትሌት መዲና ኢሳ በቀዳሚነት አጠናቃለች።
አትሌት ፎትየን ተስፋይ የሁለተኛ ደረጃን ስትይዝ÷ አትሌት ገላ ሀምበሴ በሦስተኛነት ማጠናቀቅ ችላለች።
እንዲሁም በወንዶች የ5 ኪሎ ሜትር ውድድር…
Read More...
በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ሳሙኤል ፍሬው አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር የመሰናክል ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ሳሙኤል ፍሬው አሸንፏል።
በቻይና ዢያሚንግ ውድድር አትሌት ሳሙኤል በ8:05.61 በመግባት የቦታው ክብረወሰንና የዓመቱ የርቀቱ ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ በድንቅ ብቃት በበላይነት ማሸነፍ ችሏል።
ሞሮኳዊው የኦሎምፒክ ሻምፒዮን አትሌት ኤልባካሊን ሁለተኛ…
ከ13 ዓመታት ቆይታ በኋላ ከሌስተር ሲቲ ጋር የሚለያየው ጄሚ ቫርዲ…
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሌስተር ሲቲ የፊት መስመር ተጨዋች ጄሚ ቫርዲ ከ13 ዓመታት ቆይታ በኋላ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከሌስተር ሲቲ ጋር እንደሚለያይ ክለቡ አስታውቋል፡፡
ሌስተር ሲቲ በፈረንጆቹ 2015/16 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የቫርዲ አስተዋፅኦ ከፍተኛ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ጄሚ ቫርዲ ሌስተር ሲቲን…
አርሰናልና ክሪስታል ፓላስ ዛሬ ምሽት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል በሜዳው ኤሚሬትስ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ክሪስታል ፓላስን ያስተናግዳል።
በ66 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አርሰናል ከተከታዮቹ ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማስጠበቅ ከጨዋታው ሙሉ ሶስት ነጥብ ለማግኘት ይፋለማል።
በኦሊቨር ግላስነር የሚመራው ክሪስታል ፓላስ…
“የአሮን ራምሴ እርግማን “
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዌልሳዊው ኢንተርናሽናል የአርሰናል የቀድሞ አማካኝ ተጫዋች አሮን ራምሴ ግብ በሚያስቆጥርባቸው አጋጣሚዎች ሁሉ አንድ የዓለማችን ገናና ሰው በሠዓታት ልዩነት ሕይዎቱ ያልፋል፡፡
ይህን አጋጣሚ በተደጋጋሚ ያስተዋሉ ጋዜጠኞችም፤ “የአሮን ራምሴ እርግማን (ዘ ከርስ ኦፍ አሮን ራምሴ)” ሲሉ ይጠሩታል፡፡
አሮን ራምሴ ግብ…
ቀነኒሳ በቀለ በለንደን ማራቶን እንደማይሳተፍ አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በልምምድ ወቅት ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት በለንደን ማራቶን እንደማይሳተፍ አስታውቋል፡፡
በሩጫ ሕይወቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚደግፉትና ለሚያበረታቱት አድናቂዎች ምስጋናውን ያቀረበው አትሌት ቀነኒሳ÷ አሁን ላይ ከደረሰበት ጉዳት ለማገገም ትኩረቱን እንደሚያደርግ ገልጿል።
አትሌት ቀነኒሳ…
የዞን አምስት ወርልድ ቴኳንዶ ውድድር ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሁሉም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተሳተፉበት የዞን አምስት ወርልድ ቴኳንዶ ውድድር መካሄድ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ያዘጋጀው ይህ ውድድር በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ እየተካሄደ ነው።
ውድድሩ በጁንየር፣ በካዴትና በሲንየር ተለይቶ በሶስት ምድቦች እየተካሄደ መሆኑን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ…