ስፓርት
ማንቸስተር ሲቲ ዎልቭስን 4 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ከሜዳው ውጪ የተጫወተው ማንቸስተር ሲቲ ዎልቭስን 4 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በተደረገው ጨዋታ ሃላንድ ሁለት ግቦችን ሲስቆጥር ሬይንደርስ እና ቼርኪ ቀሪ ግቦችን አስቆጥረዋል፡፡
ትናንት በጀመረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር የሊጉ ሻምፒዮኑ ሊቨርፑል ቦርንማውዝን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በዛሬው ዕለት በተካሄዱ ጨዋታዎች ደግሞ ቶተንሃም በርንሌይን፣ ሰንደርላንድ…
Read More...
በፖላንድ ሲለሲያ ዳይመንድ ሊግ የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤምሲ) በፖላንድ ሲለሲያ ዳይመንድ ሊግ የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ አምስተኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዘገብ አሸንፋለች።
አትሌቷ ተቃናቃኟን ኬኒያዊቷ ቢያትሪስ ቼቤት በፍጹም የበላይነት በመቅድም ነው በቀዳሚነት ውድድሩን ያጠናቀቀችው።
ጉዳፍ ውድድሩን በሶስት ደቂቃ ከ50 ሴኮንድ ከ62 ማይኮሮ ሴኮንድ…
አስቶን ቪላ እና ኒውካስል ዩናይትድ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶን ቪላ እና ኒውካስል ዩናይትድ ያለምንም ግብ አቻ ተለያዩ፡፡
ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ አስቶን ቪላ በሜዳው ቪላፓርክ ኒውካስልን አስተናግዷል።
በጨዋታው ኤዝሪ ኮንሳ በሰራው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
የተጫዋች ብልጫ የነበረው ኒውካስል ያገኘውን…
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 5 ጨዋታዎች ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ አምስት ጨዋታዎች ይካሄዳሉ፡፡
ትናንት የተጀመረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታዎች ዛሬ ቀጥለው ሲካሄዱ ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ አስቶን ቪላ ከኒውካስል ጋር ይገናኛል።
እንዲሁም ባለፈው የውድድር ዓመት በሊጉ ደካማ እንቅስቃሴ…
አጓጊው የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ …
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2025/26 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት የአምናው የሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል ከቦርንማውዝ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል፡፡
የ2024/25 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሊቨርፑል አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ለወራት ቡድናቸውን ሲያጠናክሩ ቢቆዩም አሁንም እያጠናከሩ ይገኛሉ፡፡
እንደ…
ሪያል ማድሪድ ፍራንኮ ማስታንቱኖን በይፋ አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ አርጀንቲናዊውን ተጫዋች ፍራንኮ ማስታንቱኖ ከሪቨር ፕሌት ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
የስፔኑ ክለብ ለአርጀንቲናዊው አማካይ ዝውውር 45 ሚሊየን ዩሮ ወጪ አድርጓል፡፡
የ18 ዓመቱ ተጫዋች በልደቱ ቀን ለስድስት ዓመታት በሳንቲያጎ በርናባው የሚያቆየውን ውል ፈርሟል፡፡
ማስታንቱኖ በዚሁ ወቅት፥ የዓለማችን…
ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እና ኦሜጋ ጋርመንት በትብብር ለመስራት ተስማሙ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እና ኦሜጋ ጋርመንት በትብብር ለመስራት የጋራ ስምምነት አድርገዋል፡፡
በኹነቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን በጋራ ለመስራት ከስምምነት ደርሰዋል፡፡
ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በ13 የሬዲዮ ጣቢያዎች፣ በሁለት የቴሌቪዥን ቻናሎች እና በበርካታ የማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች በሀገር ውስጥ…