ስፓርት
ኒውካስል ዩናይትድ ቼልሲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኒውካስል ዩናይትድ ቼልሲን 2 ለ 0 በማሸነፍ ደረጃውን አሻሻለ፡፡
በሴንት ጄምስ ፓርክ በተደረገው ጨዋታ ሳንድሮ ቶናሊ እና ቡሩኖ ጉማሬሽ አስቆጥረዋል፡፡
በጨዋታው የቼልሲው አጥቂ ኒኮላስ ጃክሰን በኒውካስሉ ተከላካይ ሲቬን ቦትማን ላይ በሰራው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል፡፡
የጨዋታውን ውጤት ተከትሎ የአሰልጣኝ ኤዲ ሆው ቡድን ኒውካስል ነጥቡን ወደ 66 ከፍ በማድረግ 3ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ቼልሲ በነበረበት 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
Read More...
ፋይዳ ለኢትዮጵያ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የብሔራዊ መታወቂያን ግንዛቤ ማሻሻልን አላማው ያደረገው የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ዛሬ በመስቀል አደባባይ ተደርጓል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ ባስጀመሩት በዚህ ውድድር 25 ሺህ ሰዎች የተሳተፉ ሲሆን ከ400 በላይ አትሌቶች የተሳተፉበት ውድድር በሁለቱም ጾታ ተደርጓል።
በወንዶቹ ውድድር…
ሊቨርፑል በአርሰናል የክብር አቀባበል ይደረግለታል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ አርሰናልን ያስተናግዳል።
የሊጉ ጨዋታ ሳይጠናቀቅ አስቀድሞ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠዉ ሊቨርፑል በዛሬው ጨዋታ ወደ ሜዳ ሲገባ በተጋጣሚዉ አርሰናል የክብር አቀባበል ይደረግለታል።
በ82 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ…
ባህር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ መድንን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ መድንን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ቀን 10:00 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ሰው ሰራሽ ሜዳ በተካሄደው ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ ሙጂብ ቃሲም እና ሔኖክ ይበልጣል ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
ኢትዮጵያ መድህን ከሽንፈት…
ሞሐመድ ሳለህ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሆኗል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ግብጻዊው የሊቨርፑል ተጫዋች ሞሐመድ ሳላህ በእግር ኳስ ፀሐፊዎች ማኅበር የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን አሸንፏል፡፡
ሳላህ በውድድር ዓመቱ 28 ግቦችን በማስቆጠርና 18 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል ሊቨርፑል የፕሪሚየር ሊጉ አሸናፊ እንዲሆን አስችሏል፡፡
በተጨማሪም በአንድ የውድድር ዓመት ብዙ የጎል ተሳትፎ ክብረ…
ሐዋሳ ከተማ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሐዋሳ ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የሐዋሳ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ታፈሰ ሰለሞን በመጀመሪያው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል፡፡
ሐዋሳ ከተማ ወደ ድል ሲመለስ ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት ሦስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ውጤቱን ተከትሎም…
ማንቼስተር ዩናይትድ ከአትሌቲክ ቢልባኦ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዩሮፓ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ ምሽት 4 ሠዓት ላይ አትሌቲክ ቢልባኦን ያስተናግዳል።
በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ ስፔን አቅንቶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል።
በሌላ በኩል ሁለቱ ቡድኖች በሳምንቱ መጨረሻ በየሊጋቸው ባደረጉት ጨዋታ ድል…