የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ተመራጭ አየር መንገድ ሽልማትን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ2022 የአፍሪካ ተመራጭ አየር መንገድ ሽልማትን አሸነፈ፡፡
አየር መንገዱ÷ በግሎባል ትራቭል መጽሔት በተካሄደው የትራዚስ አዋርድ ነው የ2022 ተመራጭ አየር መንገድ ሽልማትን ያሸነፈው፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ተመራጭ አየር መንገድ ሽልማትን በማሸነፉ የተሰማውን ደስታ ገለጾ÷ ሽልማቱ ለተሻለ አገልግሎት አቅም እንደሚሆነው በማኅበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል፡፡