Fana: At a Speed of Life!

2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና አዛን የፍፃሜ ውድድር እየተካሄደ ነው

 

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት የሚካሄደው 2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን የፍፃሜ ውድድር በአዲስ አበባ ስታዲዬም እየተካሄደ ነው፡፡

የቁርዓንና አዛን ውድድር የጠቅላይ ምክር ቤት የስራ አስኪያጅ ተወካይ ሼይኽ ኢድሪስ ዓሊ ሑሴን 2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር ስኬት ኢትዮጵያና ልጆቿ ለቁርዓን ያላቸውን ታላቅ ክብር የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡

በጠቅላይ ምክር ቤቱ የበላይ ጠባቂነት በዘይድ ኢብኑሳቢት የቁርዓን ማሕበር ጋር የተዘጋጀው ውድድሩ በዛሬው ዕለት ፍጻሜውን ያገኛል፡፡

በአዲስ አብዱልአዚዝ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.