አንዲት ላም በአንድ ጊዜ 3 ጥጃዎችን ወለደች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ ባዮ ዚማ ቀበሌ አንዲት ላም ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ጥጃዎችን በአንድ ጊዜ መውለዷ ተሰምቷል፡፡
የላሟ ባለቤቶችም ለሁለተኛ ጊዜ በአንድ ጊዜ ሦስት ጥጃዎችን በመውለዷ ደስታ ተሰምቶናል ማለታቸውን ከዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
ላሟ እና ጥጃዎቹ በጥሩ ጤንነት ላይ መሆናቸውም ተመላክቷል፡፡