Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ታዬ ከኒውዝላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከኒውዝላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዊንስተን ፒተርስ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ በሀገራቱ መካከል ስለሚከናወኑ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚዊ ትብብሮች መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም በሰብዓዊ ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎች የሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና የባለብዙ ወገን የጋራ ጥቅሞች ላይ መክረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.